መነሻ ገጽ መቻል ሲዳማ ቡና ወደ አሸናፊነት ተመልሷል !!
መቻልሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሲዳማ ቡና ወደ አሸናፊነት ተመልሷል !!

አጋራ
አጋራ

የቀድሞ አሰልጣኙን ካሰናበተ በኋላ በአሰልጣኝ ስዩም ከበደ እየተመራ ወደ ዉጤታማነት መመለስ ችሎ የነበረዉ እና ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተከታታይ በሀዋሳ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ሽንፈት አስተናግዶ የነበረዉ ሲዳማ ቡና በዘጠነኛው ሳምንት የሊጉ መርሐግብር ቀን 10:00 ሰዓት ላይ በተደረገዉ ጨዋታ በአማካዩቹ ፍሬዉ ሰለሞን እና ሙሉአለም መስፍን (ዴኮ) ግቦች ታግዞ መቻልን ሁለት ለዜሮ በሆነ ዉጤት በማሸነፍ ወደ ድል መመለስ ችሏል።

በተጠበቀዉ ልክ ዉጤታማ መሆን ያልቻለዉ እና ካለፉት አራት የሊጉ ጨዋታዎች አንዱንም ማሸነፍ ያልቻለዉ የአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ቡድን መቻል በስምንተኛው ሳምንት የሊጉ መርሐግብር ብር ከአምናዉ ሻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ዉጤት ማጠናቀቃቸው የሚታወስ ሲሆን ፤ በዛሬዉ ዕለትም በቀደመ ብቃቱ ላይ በማይገኘዉ ሲዳማ ቡና ሽንፈትን አስተናግዷል።

የዛሬዉን የዘጠነኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ ዉጤት ተከትሎም ሲዳማ ቡና በ10 ነጥብ በጊዜያዊነት 9ነኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ሲችል ፤ በተቃራኒው በዛሬው ዕለት ሽንፈት ያስተናገደዉ መቻል በስምንት ነጥብ እና በአምስት የግብ ዕዳ 12ተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

በቀጣይ በአስረኛ ሳምንት የሊጉ መርሐግብርም በዛሬዉ ጨዋታ ሽንፈት ያስተናገደዉ መቻል ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሲገናኙ ፤ የአሰልጣኝ ስዩም ከበደዉ ሲዳማ ቡናም ከፋሲል ከነማ ጋር የሚገናኙ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...