በኢትዮጵያ መድን አመራሮች አሳማኝ ባልሆነ መንገድ የተሰናበተው አሰልጣኝ በጸሎት ልዑልሰገድ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ለማሰልጠን ተስማማ።
ከታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ መድንን ከከፍተኛ ሊግ አሳድጎ ኮንትራቱ በመጠናቀቁ አይታደስልህም ተብሎ የተሰናበተው አሰልጣኙ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አመራሮች ጋር ከተነጋገረ በኋላ ክለቡን ወደ ፕሪሚየር ሊግ የማሳደግ ሃላፊነቱን ለመቀበል ተስማምቷል።
የክለቡ አመራሮችና አሰልጣኙ በኮንትራቱና በሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ዙሪያ በነገው ዕለት እንደሚነጋገሩ ከታማኝ ምንጭ የደረሰው መረጃ ያስረዳል።