By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የመቻል 80ኛ አመት ክብረ በዓል በያዝነው የሰኔ ወር እንደሚከበር ይፋ ሆነ
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችመቻል

የመቻል 80ኛ አመት ክብረ በዓል በያዝነው የሰኔ ወር እንደሚከበር ይፋ ሆነ

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
Share
SHARE

“የዳኝነት ስህተት በእግርኳሱ የሚያጋጥም ነው መነጋገሪያ ማድረግም አይገባም”

ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን

“ትልልቅ ሰዎች ያሉበት ጠንካራ ስራ የሚሰራበት እንዴት የኢትዮጵያ ስፖርት ይደግ የሚል እሳቤ ያላቸው መሪዎች በመኖራቸው ተደስቻለሁ”

ዶ/ር ሰይፉ ጌታሁን
/ የቦርድ ሰብሳቢ/

- ማሰታውቂያ -

“በመቻል የኢትዮጵያን ስፖርት ታሪክ እንቀይራለን ብዬ አምናለሁ ያንንም ለማድረግ እየሰራን ነው ነገር ግን የማያሰራ ነገር ካለ ጥለን ነው የምንሄደው”

አቶ ጸሃዬ ሽፈራው
/የቦርዱ ም/ል ሰብሳቢ/

“የግብ ጠባቂዎችን አቅም ለማሳደግ ስልጠና ሲዘጋጅ የሌሎች ክለቦችም ባለሙያዎች ይገኛሉ ለዚህ ነው መቻል ለኢትዮጵያ የምንለው”

የፊፋ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ
/ የክለቡ ቴክኒካል ዳይሬክተር/

“ደጋፊውን የተነጠቀ.. የተረሳ …ላለመውረድ የሚጫወት ብር የሚያዋጣ ሰራዊቱ የሚወክለው ቡድን እንዳለ ያላወቀውን መቻልን ወደቀደመ ስሙ መመለስ የግድ ነው” ሲሉ ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ተናገሩ።

የመቻል 80ኛ ዓመት ክብረ በዓል ከ ሰኔ 1-30/2016 ድረስ “መቻል ለኢትዮጵያ ” በሚል መሪ ቃል በይፋ እንደሚከበር በመኮንኖች ክበብ ትላንት መግለጫ የተሰጠ ሲሆን የመቻል ስፖርት ክለብ የቦርድ አባል ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው እንደገለጹት ” በፕሪሚየር ሊጉ ሁለተኛ የመሆናችን የተሰራው ጠንካራ ሪፎርም ውጤት ማምጣት መጀመሩ ነው ከዚህ በፊት የነበሩት ቦርዶች የአቅማቸውን ሰርተዋል። እንደ ቦርድ ግን ቡድኑን ለማጠናከር ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ማለት አይቻልም ይሄ ቦርድ ግን ጠንካራ ስራ ሊሰራ ተዘጋጅቷል” ሲሉ ጄኔራሉ ተናግረዋል።

መቻል በዳኞች እየተበደለ ነው በሚለው ዙሪያ ጄኔራሉ በሰጡት አስተያየት ” የዳኝነት ስህተት መላው አለም ላይ ያለ የነበረ የሚኖር በመሆኑ እንደ ችግር አናየውም እንኳን እኛ ሀገር ቀርቶ በመላው አለምም ዳኛ እየተደገፈም ይሳሳታል በእ መነጋገሪያ ማድረግም አይገባም” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

መቻልን ከሰራዊቱ በላይ ህዝቡ ይደግፈዋል የሚለው እውነት ነው ሰራዊቱ ምን አውቆ ይደግፍ ይሄ ሆን ብሎ የታቀደ ነው ሰራዊቱን ከመቻል የመለየት ስራ ተሰርቷል።
80ኛ አመት ክብረ በዓላችንን የምናከብረው የተዛነፈውን ታሪካችን ለማደስና ለማስተካከል ነው እንደ እኛ መቻል የህዝብ ነው መቻልን መደገፍ ማጀገን ሰራዊቱን ማበርታት ነው ህዝቡ ከእኛ ጎን መሆን አለበት ሲሉም ተናግረዋል።

የቦርዱ ም/ል ሰብሳቢና የአዋሽ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ጸሃዬ ሽፈራው በበኩላቸው” መቻል ውስጥ ውጤት ለሜምጣት ጠንክረን እንሰራለን አስካሁንም ጥሩም እየሰራን ነው ቁርጠኛ አቀምም ይዘን እየሰራን ነው ነገር ግን የማያሰራ ነገር ካለ ግን ጥለን ነው የምንሄደው….. በመቻል የኢት ስፖርት ታሪክ እንቀይራለን ብዬ አምናለሁ ሰፊ ታሪክ ስኬታማ የሆነ ክለብ ነው ከሀገር አልፈን በአፍሪካ ምርጡን ክለብ እናሳያለን” ሲሉ ተናግረዋል ።

የክለቡ የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ሰይፉ ጌታሁንም እንደተናገሩት ለሌሎች ክለቦች ትምህርት የሚሆን አደረጃጀት ለመፍጠር እየሰራን ነው …ቦርዱ ቁርጠኛ አቋም አለው አመራሮች ስለ አደረጃጀትና ስለ ቀጣይ ዘመኑ በማሰብ ትልቅ ሀይል ፈጥረናል በዚህም ደስተኛ ነን… ትልልቅ ሰዎች ያሉበት ጠንካራ ስራ የሚሰራበት እንዴት መቻል ይደግ የኢትዮጵያ ስፖርት እንዴት ይቀየር የሚል እሳቤ ያላቸው መሪዎች በመኖራቸው ተደስቻለሁ የእግርኳስ ቡድኑን ምርጥ ቡድንና ኮከብ ተጨዋች የሚመጣበት ለማድረግ እየሰራን ነው” ሲሉ አስረድተዋል።

የቡድኑ ቴክኒካል ዳይሬክተር የፊፋ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ቡድኑን ጠንካራ ለማድረግ ጠንክረን እየሰራን ነው የ80ኛ አመት መታሰቢያ ክብረ በአል አንዱ አካል የሆነው ኢንተርናሽናል ውድድር አዘጋጅቷል። ሀምሌ 7/2016 የኡጋንዳው ኪታራ ከመቻል ጋር ባለሀብቶች ከባለስልጣናት አርቲስቶች ከመቻል የቀድሞ ተጨዋቾችና የብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች ጋር ይጫወታሉ” ብሏል።

ከባለሙያ ማብቃት ጋር ተያይዞ የካፍ ዲ ላይሰንስ በመቻል ጠያቂነት የሚሰጥ ሲሆን ከወንድ ቡድናችን 5.ከሴቶች ደግሞ .3 ሴቶች ስልጠና ይወስዳሉ ከሌሎች ክለቦች ባለሙያዎችም መጥተው እንዲወስዱ እናደርጋለን እንደ ሀገር ያለብንን የግብ ጠባቂዎች ችግር ለመቅረፍ የራሳችንን ግብ ጠባቂዎችን አቅም ለማሳደግ ስልጠና የሚዘጋጅ ሲሆን የሌሎች ክለቦችም ባለሙያዎች እንዲገኙ እናደርጋለን ለዚህ ነው መቻል ለኢትዮጵያ የምንለው ሲል ተናግሯል።

በ80ኛ አመት ክበረ በአል ላይ 35 ሺህ ሰው የሚሳተፍበት የሩጫ ውድድር የተዘጋጀ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ የሩጫውና የደጋፊው ማሊያ ሽያጭ መጀመሩ ታውቋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article ” የተጨዋቾች ደመወዝ አለመክፈል የሆቴል ክፍያ አለመፈጸምና ሰርቪሳቸውን ማስያዝ የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ችግር ነው” አቶ ክፍሌ ሰይፈ /የአክሲዮን ማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ/
Next Article በ2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የዋንጫና የደረጃ ጨዋታዎች የዳኞችና የታዛቢዎች ሪፖርትን በመመልከት የተላለፉ ውሳኔዎች

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች |Livescore|በቀጥታ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 9 years ago
የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ረተዋል
“ሲዳማ ቡና ሲያሸንፍ የሲዳማ ህዝብ ነው፣ ሲሸነፍ ቡድኑ የመንግሥቱ ነው” አቶ መንግሥቱ ሳሳሞ /ተሰናባቹ የሲዳማ ቡና ፕሬዚዳንት/
ፌደሬሽኑ በወልዋሎ ሜዳ ዙሪያ ምላሽ ሰጥቷል።
የሱዳን ብሔራዊ ቡድን አዲስ አበባ ገብቷል !
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?