By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ጥሩ ፉክክር የታየበት የፈረሰኞቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስባህርዳር ከተማ

የጨዋታ ዘገባ | ጥሩ ፉክክር የታየበት የፈረሰኞቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር የ26ኛው ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ከአናት የተቀመጡትን ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ባህርዳር ከተማን አገናኝቶ 2 – 2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል ።

በአሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ የሚመሩት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በ27ኛው ሳምንት ለገጣፎ ለገዳዲን በረቱበት ጨዋታ ላይ በነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ ላይ ሁለት ለውጦችን በማድረግ በባህሩ ነጋሽ እና አማኑኤል ተርፉ ምትክ ቻርለስ ሉክዋጎ እና ፍሪምፖንግ ሜንሱህ ተክተው ገብተዋል ። በአሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛው በሚመራው ባህርዳር ከተማ በኩልም በተመሳሳይ በሳምንቱ መቻልን በረቱበት ጨዋታ ላይ ከነበረው ምርጥ 11 አንድ ለውጥ ብቻ በማድረግ በፉዓድ ፈረጃ ምትክ ቻርለስ ሪባኑን ተክተው ወደ ጨዋታው ገብተዋል ።

በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ የተጀመረው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊሶች ኳስን ከኋላ መስርተው ለመውጣት ጥረት በማድረግ የጀመሩት ሲሆን በባህርዳር ከተማ በኩል ተጭነው ወደ ፊት በመጠጋት አንድም ፈረሰኞቹ ኳሱን መስርተው እንዳይወጡ እንዲሁም በሚነጠቁ ኳሶች ወድያውኑ የግብ ዕድል ለመፍጠር ጥረቶችን ሲያደርጉ ተስተውሏል ።

ኳሱን ይዘው ከሜዳቸው ለመውጣት የተቸገሩት ፈረሰኞቹ የመጀመሪያ የግብ ዕድል ለመፍጠር በቻሉበት 14ኛው ደቂቃ ላይ ኳስ እና መረብን አገናኝተዋል ።

- ማሰታውቂያ -

ቢንያም በላይ ከቀኝ አቅጣጫ በአየር ያሻገረውን ኳስ ተጠቅሞ ቸርነት ጉግሳ በግንባር በመግጨት ቅዱስ ጊዮርጊስን መሪ ማድረግ ችሏል ።

ከግቡ መቆጠር ሰከንዶች በኋላ የቢንያም እና የቸርነት ጥምረት ዳግም የታየበት የግብ ሙከራ አጋጣሚ በፋሲል ገብረሚካኤል ግብ ከመሆን ድኗል ።

ከግቡ በኋላ የጣና ሞገዶቹ በይበልጥ ተጭነው በመጫወት የአቻነት ግብ ፈልገዋል ። በቀላሉ ለመስበር የማይቻለው እና በውድድር አመቱ በ26 ጨዋታዎች 17 ግቦችን ብቻ ያስተናገደው የቅዱስ ጊዮርጊስ የኋላ መስመር እስከ 30ኛው ደቂቃ ድረስ ጠንካራ የግብ ዕድሎች እንዳይፈጠሩ ማድረግ ችለዋል ።

በ30ኛው ደቂቃ ላይ ግን ድንቅ የውድድር አመትን እያሳለፈ የሚገኘው አለልኝ አዘነ ቀደም ባሉ ጨዋታዎች ላይ ያስቆጥር የነበረው አይነት ግብ በቻርለስ ሉክዋጎ መረብ ላይ አሳርፏል ።

አለልኝ አዘነ ከሳጥኑ ውጪ ከቻርለስ ሪባኑ የደረሰውን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ በመምታት ነው የጨዋታውን ውጤት ወደ 1 – 1 ለመቀየር የቻለው ።

በቀጣዮቹ የመጀመሪያው አጋማሽ ደቂቃዎች ላይ ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ ያስመለከተን ጨዋታ አጋማሹ ከመጠናቀቁ በፊት ሌላ ግብ አስተናግዷል ።

በቅዱስ ጊዮርጊስ የሜዳ ክፍል በግራ አቅጣጫ የተገኘውን የቅጣት ምት ፍራኦል መንግስቱ በግራ እግሩ ወደ ግብ ሲያሻግር በናትናኤል ዘለቀ ጭንቅላት ተጨርፎ ከመረብ ላይ አርፏል ።

የመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታው ክፍለጊዜም በባህርዳር ከተማ የ2 – 1 መሪነት ተጠናቀቀ ።

በሁለተኛው አጋማሽ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመሀል የሜዳው ክፍል ላይ በአንፃራዊነት የተወሰደባቸውን ብልጫ ለመመለስ በሚመስል መልኩ ጋቶች ፓኖምን በሀይደር ሸረፋ ተክተው ጨዋታውን ጀምረዋል ።

አጋማሹን በተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ የጀመሩት ፈረሰኞቹ በተለይም በመጀመሪያው አጋማሽ እንቅስቃሴው እምብዛም በነበረው አቤል ያለው አማካኝነት ተደጋጋሚ የማጥቃት አጋጣሚዎች ለመፍጠር ችለዋል ።

ከአቤል ያለው ባሻገር በ47ኛው ደቂቃ ላይ በግራ መስመር የነበረው ቸርነት ጉግሳ ወደ ሳጥን ይዞ የገባውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ለእስማኤል ኦሮ አጎሮ ለማቀበል ያደረገው ሙከራ በፋሲል ገ/ሚካኤል ተይዟል ።

በ50ኛው ደቂቃ ላይ ግን ፈረሰኞቹ ግብ አስቆጥረዋል ። አቤል ያለው ! 10 ቁጥር ለባሹ አቤል ያለው ከቢንያም በላይ የተቀበለውን ኳስ በግቡ የቀኝ ቋሚ አስታኮ በመምታት በፋሲል ገብረሚካኤል መረብ ላይ አሳርፏል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ ፈረሰኞቹ በይበልጥ በሁለቱ መስመሮች ለመጠቀም ጥረቶችን ቢያደርጉም ውጤታማ አልነበሩም ። በተጨማሪም የሊጉን ኮከብ ግብ አስቆጣሪ እስማኤል ኦሮ አጎሮን ኢላማ ያደረጉ ኳሶች ወደ ፊት ቢላኩም በተደጋጋሚ ከጨዋታዉ ውጪ ሆነዋል ።በባህርዳር ከተማ በኩል በተለይም እንደ አደም አባስ ፣ ፉዓድ ፈረጃ እንዲሁም ማማዱ ሲዲቤ አይነት የማጥቃት ሚና ያላቸውን ተጫዋቾች ቀይረው በማስገባት ተጨማሪ ግብ ለማግኘት ጥረቶችን አድርገዋል ።

የጣና ሞገዶቹ በአለልኝ አዘነ እና በፉዓድ ፈረጃ ካደረጓቸው ያልተሳኩ የቆሙ ኳስ ሙከራዎች ባለፈም በፍራኦል መንግስቱ ወደ ግብ ተሻግሮ ሉክዋጎ ባወጣው ኳስ የግብ አጋጣሚዎች ለመፍጠረ ችለዋል ።

በ87ኛው ደቂቃ ላይም በፈጣን እንቅስቃሴ ማማዱ ሲዲቤ ከቀኝ አቅጣጫ ወደ መሀል የቀነሰውን ኳስ ፉዓድ አግኝቶ ወደ ግብ መሞከር ቢችልም ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል ።

በ90+1 ደቂቃ ላይ የፈረሰኞቹ የመሀል ተከላካይ ፍሪምፖንግ ሜንሱህ በፈጣን የመልሶ ማጥቃት ሂደት ከግራ አቅጣጫ ለአጎሮ ለማድረስ የላከው ኳስ በያሬድ ባየህ ተመልሷል ።

በመጨረሻም ጥሩ ፉክክር የታየበት ጨዋታው በ2 – 2 ውጤት ፍፃሜውን አግኝቷል ።

ውጤቱንም ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 59 በማድረስ መሪነቱን ሲያስቀጥል ባህርዳር ከተማ በ54 ነጥቦች ተከታዩን ደረጃ ይዟል ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ሀድያ ሆሳዕና ከሶስት ለዜሮ መመራት ተነሳስቶ ጨዋታውን በአቻ ዉጤት አጠናቋል !!
Next Article የጨዋታ ዘገባ | መቻል ወልቂጤ ከተማን ረቷል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችየትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር የሊጉን አስተዳደር ማብራሪያ ጠይቋል

Habtamu Mitku By Habtamu Mitku 11 months ago
የኡጋንዳው ክለብ ተጋባዥ የሆነበት11ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ሲቲ ካፕ ዋንጫ ቅዳሜ ይጀመራል
“ታክቲኩን ካለመተግበራችን ካልሆነ በስተቀር ከአሰልጣኝ ስዩም ጋር ምንም አይነት ችግርም ልዩነትም የለብንም፤ ዋንጫውን ከፍ አድርገን እናነሳዋለን” ሳሙኤል ዮሃንስ /ፋሲል ከነማ/
” በሚገባ አጥቅተን ከተጫወትን ዉጤታማ የማንሆንበት ምክንያት የለበትም። ( possess has to be positive )”አሰልጣኝ ስዮም ከበደ
”በታክቲክ ደረጃ በተጋነነ መልኩ ሚበልጠኝ አሰልጣኝ የለም !!” ”ምክትል በሆንክበት ቤት ዋና አሰልጣኝ ሆኖ መሾም በጣም የተለየ ስሜት አለው !!” ”መምራት ጀምረናል ከ ፈጣሪ ጋር አሸናፊ እንሆናለን !!” አሰልጣኝ ኤርምያስ ዱባለ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?