By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ሀድያ ሆሳዕና ከሶስት ለዜሮ መመራት ተነሳስቶ ጨዋታውን በአቻ ዉጤት አጠናቋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካውንት ታገደ
አትሌቲክስ ዜናዎች
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዳማ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ሀድያ ሆሳዕና ከሶስት ለዜሮ መመራት ተነሳስቶ ጨዋታውን በአቻ ዉጤት አጠናቋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 6 months ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሀያ ስምንተኛ ሳምንት ሁለተኛ ዕለት ጨዋታ ቀን ዘጠኝ ሰዓት ላይ የተገናኙት አዳማ ከተማ እና ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ሶስት አቻ በሆነ ዉጤት አጠናቀዋል።

ተመጣጣኝ በሚባል የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በጀመረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም በተለይ በሜዳዉ የመሐል ክፍል ላይ ከፍተኛ ፉክክር ያስመለከተን ሲሆን ፤ በጨዋታው መባቻ 7ተኛው ደቂቃ ላይም አዳማ ከተማ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል።

በዚህም የሀድያዉ ተከላካይ ግርማ በቀለ ዮናታን ላይ የሰራዉን ጥፋት ተከትሎ የተሰጠዉን ቅጣት ምት ረዘም ላሉ ሳምንታት በጉዳት ላይ ያሳለፈው አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በቀጥታ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ከግቧ መቆጠር በኋላ መነቃቃት ያሳዩት አዳማዎች ያስቆጠሯትን ግብ ለማስጠበቅ በሚመስል መልኩ እና የሚያገኟቸዉን አጋጣሚዎችም በቶሎ ፊት መስመር ላይ ለሚገኙት ተጫዋች በማቀበል ተጨማሪ ግብ ለማስቆጠር ሰመጥሩ ተስተውሏል።

- ማሰታውቂያ -

በተቃራኒው ጥሩ የሚባል የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ቢያስመለክቱም ግብ ማስቆጠርም ሆነ ተጠቃሽ የሚባል ሙከራን ለማድረግ የተቸገሩ የሚመስሉት ሀድያዎች አጋማሹ ሊጠናቀቅ የተወሰኑ ደቂቃዎች በቀሩበት ወቅት ተጨማሪ ግብ ተቆጥሮባቸዋል። በዚህም በ39ነኛዉ ደቂቃ ላይ የሀድያዉ ግብ ጠባቂ አሜ መሐመድ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተገኘዉን የፍፁም ቅጣት ምት ዳዋ ሁቴሳ ወደ ግብነት በመቀየር ለራሱም ለክለቡም ሁለተኛ ጎል ማስቆጠር ችሏል። ምንም እንኳን ሁለት ግብ ይቆጠርባቸዉ እንጅ በእንቅስቃሴ የተሻሉ የነበሩት ሀድያዎች ወደ ጨዋታው የሚመልሳቸውን ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ለእረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስ አጋማሹ እንደተጀመረ ወዲያውኑ አዳማ ከተማዎች ሶስተኛ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም በ47ተኛዉ ደቂቃ ላይ ደስታ ዮሐንስ ከማዕዘን ያሻማውን ኳስ ተከላካዩ አዲስ ተስፋየ በግንባሩ ወደ ግብነት በመቀየር የክለቡን መሪነት ወደ ሶስት ከፍ ማድረግ ችሏል።

ሶስተኛ ግብ ካስተናገዱ በኋላ በይበልጥ በሜዳ ላይ ጥሩ በመንቀሳቀስ ወደ ጨዋታው ለመመለስ ሲጥሩ የነበሩት ሀድያዎች በ53ተኛዉ ደቂቃ ላይ ወደ ጨዋታው የሚመልሳቸዉን ግብ በሰመረ ሀፍተይ አማካኝነት ማስቆጠር ችለዋል። ከዚች ግብ መቆጠር በኋላ ጫና መፍጠር የቻሉት ሀድያዎች ከግቧ መቅጠር  ከአስር ደቂቃ በኋላም ሁለተኛ ግብ ማግኘት ችለዋል ፤ በዚህም የአዳማዉ ተከላካይ ተመስገን ብርሀኑ ሳጥን ውስጥ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት አጥቂዉ ባየ ገዛኸኝ ወደ ግብነት በመቀየር ቡድኑን ወደ ጨዋታው መመለስ ችሏል።

ከሶስት ለዜሮ መመራት ወደ ሶስት ለሁለት ከፍ ማለት የቻሉት ሀድያዎች ከተደጋጋሚ ሙከራዎች በኋላ በ83ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሶስተኛ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ አጥቂዉ ባየ ገዛኸኝ ከርቀት አስደናቂ ግብ በማስቆጠር ክለቡ ሀድያ ሆሳዕና ከመመራት ተነስቶ ጨዋታውን ሶስት አቻ በሆነ ዉጤት እንዲያጠናቀቅ ማድረግ ችሏል። ዉጤቱን ተከትሎም ሀድያ በ40 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ፤ በተቃራኒው አዳማ ከተማ ደግሞ በ37 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

You Might Also Like

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካውንት ታገደ

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የአህመድ ሁሴን ግቦች አዞዎቹን አሸናፊ አድርገዋል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ጥሩ ፉክክር የታየበት የፈረሰኞቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Toronto marathonአትሌቲክስዜናዎች

ኢትዮጵያዊቷ ቡዜ ድሪባ የቶሮንቶ ዋተርፍሮንት ማራቶን አሸናፊ ሆነች

Mussie Girmay By Mussie Girmay 2 months ago
ለአሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ህክምና ወደ 3.8 ሚሊዮን ብር ገቢ ተደርጓል ተባለ…
ረቡዕ…ረቡዕ…ረቡዕ…ረቡዕ ሀትሪክ የመጀመሪያ ካደረጋት ባለቀለም ሀትሪክ ጋዜጣዋ በተጨማሪ ሀትሪክ በባለቀለም መፅሔትም መጣችልዎ!!
የጨዋታ ዘገባ | የጦና ንቦቹ እና አዳማ ከተማ ያደረጉት የዕለቱ የመጀመሪያ መርሐግብር በአቻ ዉጤት ተገባዷል !!
የጨዋታ ዘገባ | የአዳማ ከተማ እና የሀድያ ሆሳዕና ጨዋታ ያለምንም ግብ ተጠናቋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?