By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የአህመድ ሁሴን ግቦች አዞዎቹን አሸናፊ አድርገዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችአርባምንጭ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግለገጣፎ ለገዳዲ

የጨዋታ ዘገባ | የአህመድ ሁሴን ግቦች አዞዎቹን አሸናፊ አድርገዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከሶስት ቀናት በኋላ ወደ ውድድር ሲመለስ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታድየም በተደረገው የ28ኛው ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ አርባ ምንጭ ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲን 2 – 1 አሸንፏል ።

በ27ኛው ሳምንት ከሲዳማ ቡና አቻ የተለያዩት አርባምንጭ ከተማዎች በጨዋታው ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ ሶስት ለውጦችን በማድረግ አበበ ጥላሁን ፣ ወርቅይታደስ አበበን እና ቡጣቃ ሸመናን በአካሉ አትሞ ፣ አሸናፊ ፊዳ እና አቡበከር ሻሚል ተክተው ገብተዋል ። በሳምንቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ የተረቱት ለገጣፎ ለገዳዲዎች በበኩላቸው አራት ለውጦችን በማድረግ በተስፋዬ ነጋሽ ፣ ኤልያስ አታሮ ፣ መሀመድ አበራ እና አማኑኤል አረቦ ምትክ አቤል አየለ ፣ አስናቀ ተስፋዬ ፣ ሱራፌል አወል እና ካርሎስ ዳምጠውን ተክተው ገብተዋል ።

በጨዋታው ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት የግድ ከጨዋታዉ ሶስት ነጥቦችን ማግኘት የነበረበት አርባምንጭ ከተማ ጨዋታውን በብልጫ መጀመር ችሏል ። አዞዎቹ በተደጋጋሚም ፊት መስመር ለሚገኙ ተጫዋቾች በሚላኩ ኳሶችም የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ጥረቶች አድርገዋል ።

- ማሰታውቂያ -

አዞዎቹ ብልጫውን ወስደው በመጫወት ወደ ተጋጣሚያቸው የግብ ክልል ቶሎ ቶሎ ለመድረስ ቢጥሩም የለገጣፎ ለገዳዲ የኋላ ከፍል አልፈው ሙከራዎችን ለማድረግ ተቸግረው ቆይተዋል ።

ጨዋታው 18ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ አሸናፊ ፊዳ በሳጥን ውስጥ ሆኖ ከተመስገን ደረሰ የተላከለትን ኳስ ለመጠቀም ሲሞክር በአስናቀ ተስፋዬ በተሰራበት ጥፋት አዞዎቹ የፍፁም ቅጣት ምት አግኝተዋል ። የፍፁም ቅጣት ምቱንም አህመድ ሁሴን ከመረብ አሳርፎታል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ኳስ ተቆጣጥረው ለመጫወት ጥረቶችን አድርገዋል ።

በ35ኛው ደቂቃ ላይ ግን ለገጣፎ ለገዳዲዎች አቻ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋል ። ሱራፌል አወል ከሳጥኑ በቅርብ ርቀት የተገኘውን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ በመምታት ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

ከግቡ መቆጠር ሰከንዶች ቆይታ በኋላ አስናቀ ተስፋዬ ወርቅይታደስ አበበ ላይ በሰራው ጥፋት በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል ።

የመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለጊዜም በ1 – 1 ውጤት ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽም አርባምንጭ ከተማዎች ይበልጥ ጫና በመፍጠር ከጨዋታው ውጤት ይዘው ለመውጣት ጥረቶች ያደረጉበት ነበር ።

አዞዎቹ በተደጋጋሚ ወደ ለገጣፎ ለገዳዲ የግብ ክልል ለመድረስ ጥረቶች ቢያደርጉም የለገጣፎ ለገዳዲውን ግብ ጠባቂ ኮፊ ሜንሳህን የፈተነ የግብ ሙከራ ለማድረግ ተቸግረዋል ።

በ61ኛው ደቂቃ ላይ ግን የለገጣፎ ለገዳዲን መረብ በጨዋታው ለሁለተኛ ጊዜ ማግኘት ችለዋል ። የአርባምንጭ ከተማን ቀዳሚ ግብ ያስቆጠረው አህመድ ሁሴን ከወርቅይታደስ አበበ የተሻገረለትን ኳስ ከመረብ ላይ አሳርፏል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይም አዞዎቹ ተጨማሪ ግብ ለማከል ተጭነው ሲጫወቱ ለገጣፎ ለገዳዲዎች አብዛኛውን ጊዜያቸውን ከኳስ ጀርባ ለማሳለፍ ተገደዋል ።

በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ አርባምንጭ ከተማዎች በተለይም በኤሪክ ካፓይቶ አማካኝነት በ79ኛው ደቂቃ ላይ ያደረጉት ሙከራን ጨምሮ ሶስተኛ ግብ ማስቆጠር የሚችሉባቸውን አጋጣሚዎች መፍጠር ቢችሉም ሳይጠቀሙባቸው ቀርተዋል ።

በመጨረሻም በበረከት ደሙ በሚመራው አርባምንጭ ከተማ የ2 – 1 ድል ጨዋታው ተጠናቋል ።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ሀድያ ሆሳዕና ከሶስት ለዜሮ መመራት ተነሳስቶ ጨዋታውን በአቻ ዉጤት አጠናቋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችወልቂጤ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወልዋሎ

የጨዋታ ቅድመ- እይታ | ወልዋሎ አ.ዮ ከ ወልቂጤ ከተማ

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 6 years ago
አዲስ አዳጊዎቹ ወልቭሶች የጌታነህ ከበደ ፈላጊ ሆነዋል
​በለንደን የ16ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና  የሚሳተፉ አትሌቶች ዝርዝር  ታወቀ!!
አሰልጣኝ ዘማርያም ወልደ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከተማ ተለያዩ
“አሰልጣኝ እስማኤል አቡበከር ስለደበደበኝ ከቡድኑ አግጄዋለሁ ጥርሴም ተጎድቷል” አቶ ሲሳይ.ተረፈ /የአ/አከተማ እግርኳስ ቡድን መሪ/
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?