By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | መቻል ወልቂጤ ከተማን ረቷል
Share
Notification Show More
Latest News
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….
ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
“ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ
ዋልያዎቹ ዜናዎች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
መቻልቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወልቂጤ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | መቻል ወልቂጤ ከተማን ረቷል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 6 months ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ28ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ቀዳሚ ጨዋታ መቻል ወልቂጤ ከተማን 2 – 0 አሸንፏል ።


ወልቂጤ ከተማዎች በ27ኛው ሳምንት ከፋሲል ከነማ ነጥብ በተጋሩበት ጨዋታ ላይ አንድ ለውጥ ብቻ በማድረግ በተመስገን በጅሮንድ ምትክ ኤፍሬም ዘካርያስን አሰልፈዋል ። በመቻል በኩል በሳምንቱ በባህርዳር ከተማ በተረቱበት ጨዋታ ላይ ከነበረው ምርጥ 11 ስድስት ለውጦች በማድረግ ዳግም ተፈራ ፣ ያብስራ ሙሉጌታ ፣ ግርማ ዲሳሳ ፣ በኃይሉ ግርማ ፣ ሳሙኤል ሳሊሶ እና ምንይሉ ወንድሙን በውብሸት ጭላሎ ፣ ቶማስ ስምረቱ ፣ አህመድ ረሺድ ፣ ተስፋዬ አለባቸው ፣ ተሾመ በላቸው እና እስራኤል እሸቱ ተክተው በመግባት ጨዋታውን ጀምረዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ የሚመራው መቻል በተሻለ የጨዋታ እንቅስቃሴ ከተጋጣሚው ተሽሎ አጋማሹን አሳልፏል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃ ላይም ከነአን ማርክነህ ለሳሙኤል ሳሊሶ አመቻችቶ ያቀበለውን ኳስ ሳሙኤል አስቆጠረው ተብሎ ቢጠበቅም የግብ ሙከራው ከግቡ አናት በላይ ወጥቷል ።

- ማሰታውቂያ -

የተሻለ ጫና በመፍጠር የማጥቃት ሂደታቸውን እያጠናከሩ የሄዱት መቻሎች ተደጋጋሚ የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገዋል ። በወልቂጤ ከተማ በኩል በቀደሙት ጨዋታዎች ላይ እንደሚታየው የቡድኑን ወሳኝ ተጫዋች ጌታነህ ከበደን ኢላማ ያደረጉ ኳሶችን በፈጣን እንቅስቃሴ ወደ ፊት ለማድረስ ቢጥሩም የመቻል ተከላካዮች ያንን የፈቀዱ አልነበሩም ።

የቡድኑ አምበል ጌታነህ ከበደ በ17ኛው ደቂቃ ላይ ካደረገው ኢላማውን ያልጠበቀ የግብ ሙከራ በቀርም ዳግም ተፈራን የፈተነ የግብ ሙከራ በአጥቂውም ሆነ አጠቃላይ በቡድኑ በኩል አልተደረገም ።

በመቻል በኩልም በተደጋጋሚ ወደ ወልቂጤ ከተማ የግብ ክልል ለመድረስ የቻሉባቸውን አጋጣሚዎች መፍጠር ችለው የነበረ ቢሆንም የሚፈጠሩት የግብ ዕድሎች በጠንካራ የግብ ሙከራዎችች የታጀቡ አልነበሩም ። በ28ኛው ደቂቃ ላይ መቻሎች ቀዳሚ መሆን የቻሉበትንም የግብ ዕድል ያገኙ ቢመስሉም በረከት ደስታ ከሳሙኤል ሳሊሶ የደረሰውን ኳስ ሳይጠቀምበት ቀርቷል ።

የመጀመሪያው አጋማሽ ወደ መጠናቀቂያው ሲቃረብ በመቻል በኩል ግብ ተቆጥሯል ። የወልቂጤ ከተማው አስራት መገርሳ መዘናጋት ሚናው ከፍ ብሎ በታየበት በዚሆ አጋጣሚ ምንይሉ ወንደሙ ከከነአን ማርክነህ የተቀበለውን ኳስ በቀላሉ ከመረብ አሳርፏል ።

የመጀመሪያው አጋማሽም በመቻል የ1 – 0 መሪነት ፍፃሜውን አግኝቷል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራው ወልቂጤ ከተማ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ በተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ የአቻነቱን ግብ ለማግኘት ጥረቶች አድርገዋል ።

በተለይም በመስመሮች በሚደረጉ የማጥቃት ሂደቶች የመቻልን የኋላ ክፍል ለመፈተን ያደረጓቸው ጥረቶች በጠንካራ የግብ ሙከራዎች አልታጀቡም ።

በ64ኛው ደቂቃ ላይ ግን መቻሎች ሁለተኛ ግባቸውን አግኝዋል ። ከርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት ሳሙኤል ሳሊሶ ወደ ግብ ሲያሻግረው ግብ ጠባቂው ፋሪስ አሎው በሚገባ ሳይቆጣጠረው ቀርቶ ኳሱ የግሩም ሐጎስን ጀርባ ነክቶ ከመረብ ላይ አርፏል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልልሎች ለመድረስ የሚደረጉ ሙከራዎች እምብዛም የነበሩ ሲሆን ወደ ጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ ግን የተሻሉ የግብ ሙከራዎች በመቻልም ሆነ በወልቂጤ ከተማ በኩል ተደርገዋል ።

ነገር ግን እነዚህ ሙራዎች ወደ ግብነት ሳይቀየሩ ጨዋታት በመቻል የ2 – 0 አሸናፊነት ተጠናቋል ።

በ29ኛው ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ሰኔ 22 ሐሙስ ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ወልቂጤ ከተማ ከወላይታ ድቻ ሲጫወቱ ሰኔ 24 በተመሳሳይ ሰዓት መቻል ከኢትዮጵያ ቡና ይጫወታሉ ።

You Might Also Like

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….

“ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ጥሩ ፉክክር የታየበት የፈረሰኞቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
Next Article ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ከዳኝነት አለም ሊያገል ይሆን ?

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቃለመጠይቅቅዱስ ጊዮርጊስአብዱልከሪም ነኪማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“እግር ኳስ ሊያቀራርበን እንጂ ሊለያየን ኣይገባም” ኣብዱልከሪም ኒኪማ

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 5 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ወልቂጤ ከተማ ባህርዳር ከነማን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ 5ተኛ አሳድጓል።
አዲሴ ካሳ ከሀዋሳ ጋር ሊለያዩ ይሆን
መቐለ 70 እንደርታ ከካኖ ስፖርት ሚያደርገው ጨዋታ ቀጥታ የቴሌቪዥን ሽፋን ሊያገኝ ነው
ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትም ባለቀለሟ፣ ተወዳጇ እና ሳምንታዊዋ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገም የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛሎት ለንባብ ትቀርባለች፡፡
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?