By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የአደም አባስ ብቸኛ ግብ የጣና ሞገዶቹን አሸናፊ አድርጓል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
አዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችባህርዳር ከተማ

የጨዋታ ዘገባ | የአደም አባስ ብቸኛ ግብ የጣና ሞገዶቹን አሸናፊ አድርጓል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

በሊጉ የ24ኛ ሳምንት ሁለተኛ መርሀግብር ጥሩ አቋም ላይ የሚገኙትን አዳማ ከተማን ከባህርዳር ከተማ አገናኝቶ በባህርዳር ከተማ የ1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል ።

በ23ኛው ሳምንት ጨዋታ ከወላይታ ድቻ ነጥብ በተጋራው አዳማ ከተማ በኩል በጨዋታው ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ ሁለት ለውጦች ሲደረጉ አቡበከር ወንድሙ እና ቦና አሊ አዲስ ተስፋዬን እና አሜ መሀመድን ተክተው ወደ ሜዳ ገብተዋል ። በባህርዳር ከተማ በኩል በሳምንቱ ኢትዮጵያ ቡናን በረቱበት ጨዋታ ላይ በነበረው ምርጥ 11 ላይ ምንም ለውጥ ሳያደርጉ ጨዋታውን ጀምረዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ የአሰልጣኝ ይታገሱው አዳማ ከተማ በኳስ ቁጥጥርም ሆነ ወደ ግብ ቀርቦ የግብ ዕድሎች በመፍጠር ረገድ የተሻለ ነበር ።

- ማሰታውቂያ -

በባህርዳር ከተማ በኩል በተወሰደባቸው ብልጫ የመልሶ ማጥቃት ሂደቶች ለመጠቀም የተገደዱ ቢሆንም እንዚህ እንቅስቃሴዎች ያን ያህል ለአዳማ ከተማ ተጫዋቾች ፈታኝ አልነበሩም ።

በ8ኛው ደቂቃ ላይ ቦና አሊ ከርቀት አክርሮ ወደ ግብ የመታው እና በፋሲል ገብረሚካኤል የተያዘው ኳስ የጨዋታው ቀዳሚ የግብ ሙከራ ነበር ።

በጨዋታው 12ኛ ደቂቃ ላይ አማኑኤል ጎበና ጉዳት ማስተናገዱን ተከትሎ በቢንያም አይተን ተቀይሮ ከሜዳ ለመውጣት ተገዷል ።

በ14ኛው ደቂቃ ላይም ተቀይሮ በገባው ቢንያም አይተን ላይ በተሰራ ጥፋት የተገኘውን የቅጣት ምት ዮሴፍ ታረቀኝ በጠንካራ ምት ወደ ግብ የላከው ኳስ የግቡን አግዳሚ ለትሞ ወጥቷል ።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላም ዮሴፍ ታረቀኝ በጨዋታ እንቅስቃሴ ከሳጥን ውጪ ያደረገው የግብ ሙከራ በፋሲል ገብረሚካኤል ተይዟል ።

በጣና ሞገዶቹ በኩል የሚደረጉት የመልሶ ማጥቃት እንቅስቃሴዎች አንድም ጠንካራ የግብ ዕድል ለመፍጠር ሲሳናቸው በ21ኛው ደቂቃ ላይ በፍራኦል ተስፋዬ ከቅጣት ምት በተሞከረ ኢላማውን የጠበቀ ኳስ የመጀመሪያውን ሙከራ አድርገዋል ።

በቀጣዮቹ የመጀመሪያው አጋማሽ ቀሪ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ግብ ጠባቂዎቹን የፈተነ የግብ ሙከራ ሳይታይ ቢቆይም በመጨረሻ ላይ ፍፁም ጥላሁን ሳይጠቀምበት የቀረው ኳስ ምናልባትም የጣና ሞገዶቹን አጋማሹን በመሪነት ማጠናቀቅ የሚያስችል ነበር ።

ተመጣጣኝ የሆነ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በታየበት የሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በሁለቱም በኩል ከጨዋታው ሶስት ነጥብ ይዘው ለመውጣት ጥረቶች የተደረጉበት ነበር ።

በአጋማሹ ቀዳሚው የግብ ሙከራም በአዳማ ከተማ በኩል ሲደረግ ቦና አሊ ያደረገውን ጠንከር ያለ የግብ ሙከራ በፋሲል እጆች ላይ አርፏል ።

በአዳማ ከተማም ሆነ በባህርዳር ከተማ ዘንድ የተደረጉት የግብ አጋጣሚዎች የማግኘት እንቅስቃሴዎች በግብ ሙከራዎች ሳይታጀቡ ቢቆዩም መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ አስራ አንድ ያህል ደቂቃዎች ሲቀሩ ጨዋታው ግብ ተቆጥሮበታል ። ባህርዳር ከተማ ! አደም አባስ !

በአጋማሹ ተቀይሮ የገባው አደም አባስ ከዱሬሳ ሹቢሳ የደረሰውን ኳስ በ79ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፎታል ።

በቀጣዮቹ የጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ አዳማ ከተማዎች ተጭነው በመጫወት የግብ ዕድሎችን ለማግኘት ጥረት ቢያደርጉም ኳስ እና መረብን ማገናኘት ሳይችሉ ጨዋታው በባህርዳር ከተማ የ1 – 0 አሸናፊነት ፍፃሜውን አግኝቷል ።

በ25ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ግንቦት 12(ቅዳሜ) ከ9:00 ጀምሮ አዳማ ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ ሲጫወት በተከታዩ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ባህርዳር ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ይጫወታል ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ቡናማዎቹ ወደ አሸናፊነት ተመልሰዋል !!
Next Article 52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፕዮና ከማክሰኞ ጀምሮ ይደረጋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር ለመቅጠር ባወጣው የስራ ማስታወቂያ መሠረት ከፍተኛ ነጥብ ያስመዘገቡ ተወዳዳሪዎች

Fitsum Nigusse By Fitsum Nigusse 3 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ሰበታ ከተማ የውድድር አመቱ ሶስተኛ ድሉን እስመዝግቧል
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ ለሁለት ቀናት በአርባምንጭ ከተማ ተካሂዶ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል
ኢትዮጵያ ቡና ምክትል አሰልጣኝ ቀጠረ !
ሽመልስ በቀለ ወደ አዲስ ክለብ አምርቷል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?