መነሻ ገጽ ለንደን ማራቶን አትሌት ሲፋን ሀሰን በለንደን ማራቶን አሸንፋለች
ለንደን ማራቶንአትሌቲክስዜናዎች

አትሌት ሲፋን ሀሰን በለንደን ማራቶን አሸንፋለች

አጋራ
አጋራ

በዛሬው ዕለት በተደረገው 43ኛው የለንደን ማራቶን በዜግነት ኔዘርላንላዊ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን በመጀመሪያ የማራቶን ውድድሯ 2:18:33 በመግባት አሸንፋለች ።

የአትሌቷ አሸናፊነት በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን ያስገኘላት ሲሆን በተለይም በውድድሩ ለሁለት ያህል ጊዜያቶ በህመም ምክንያት የምታቋርጥ በሚመስል መልኩ ወደ ኋላ ብትቀርም በመጨረሻም ራሷን ከፊት አግኝታለች ።

በወድድሩ የአምናው የለንደን ማራቶን አሸናፊዋ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው ፣ አትሌት መገርቱ አለሙ ፣ አትሌት ፔሬስ ጄፕቺርቺር እና አትሌት ሼልያ ቼፕኪሩይ ሲመሩ ቢቆዩም አትሌት ሲፋን ከኀላ በመድረስ በድንቅ አጨራረስ የውድድሩ አሸናፊ ሆናለች ።

አትሌት ሲፋንን በመከተል አትሌት መገርቱ አለሙ በ2:18:37 ሁለተኛ ፣ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው 2:18:53 ፣ አትሌት አልማዝ አያና በ2:20:44 እንዲሁም ታዱ ተሾመ በ2:21:31 ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።

በወንዶቹ ውድድር ኬንያዊው አትሌት ኬልቪን ኪፕቱም በ2:01:25 በመግባት የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ጨምር አሸናፊ ሆኗል ።

የአለም ሻምፕየኑ አትሌት ታምራት ቶላ በ2:04:59 በሶስተኝነት ሲያጠናቅቅ አትሌት ልዑል ገብረስላሴ በ2:05:45 እንዲሁም አትሌት ሰይፉ ቱራ በ2:06:38 በአምስተኝነት ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...