By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ ሀዋሳ ከተማን አሸንፏል
Share
Notification Show More
Latest News
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….
ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
“ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ
ዋልያዎቹ ዜናዎች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሀዋሳ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየጨዋታ ዘገባድሬዳዋ ከተማ

የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ ሀዋሳ ከተማን አሸንፏል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 7 months ago
Share
SHARE

በሊጉ የ20ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ሀዋሳ ከተማን አሸንፏል ።

በድሬዳዋ ከተማ በኩል በ19ኛው ሳምንት በባህርዳር ከተማ በተረቱበት ጨዋታ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አምስት ለውጦችን አድርገው ገብተዋል ። አሳንቴ ጎድፍሬድ ፣ አሰጋኸኝ ጴጥሮስ ፣ ብሩክ ቃልቦሬ ፣ አቤል አሰበ እና ሄኖክ ሀሰን ምትክ
መሳይ ጳውሎስ ፣ እንየው ካሳሁን ፣ ዮሴፍ ዮሀንስ ፣ ዳዊት እስጢፋኖስ እና ጋዲሳ መብራቴ በመጀመሪያው አሰላለፍ ተካተዋል ።

በሀዋሳ ከተማ በኩል ደግሞ ወልቂጤ ከተማን ከረቱበት ጨዋታ ሶስት ለውጦችን በማድረግ በመድኃኔ ብርሀኔ ፣ አዲሱ አቱላ እና ሙጂብ ቃሲም ምትክ አብዱልባሲጥ ከማል ፣ ዳንኤል ደርቤ እና እዮብ አለማየሁ በምርጥ 11 አካተዋል ።


ቀዝቀዝ ባለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የጀመረው ጨዋታ በአንፃራዊነት ሀዋሳ ከተማዎች የተሻሉ ሆነው የታዩበት ነበር ።

- ማሰታውቂያ -

ድሬዳዋ ከተማዎች በተወሰኑ አጋጣሚዎች ወደ ፊት ለመድረስ ጥረት ከማድረጋቸው ውጪ ይህ ነው ሊባል የሚችል ዕድል አልፈጠሩም ።

በሀዋሳ ከተማ በኩል ሁነኛ የፊት አጥቂያቸው ሙጂብ ቃሲም አለመኖር በተወሰኑ መልኩ በማጥቃት ላይ ክፍተት እንደፈጠረባቸው ማሳያዎች ነበሩ ።

በጨዋታው ቀዳሚ የግብ ሙከራ በ17ኛው ደቂቃ ላይ የተደረገ ሲሆን አሊ ሱሌማን የድሬዳዋ ከተማ ተከላካዮችን አልፎ ኳስ እና መረብን ለማገናኘት ያደረገው ጥረት ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል ።

ከአስር ደቂቃዎች በኋላም ኤርትራዊው አጥቂ አሊ ሱሌማን ከበቃሉ ገነነ የደረሰውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቶበታል ።

የመጀመሪያው አጋማሽን ግብ ሳይቆጠርበት 0 – 0 ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የተሻሉ ሆነው የታዩት ደግሞ ድሬዳዋ ከተማዎች ነበሩ ። ብርቱካናማዎቹ የተሻለ ጫና ፈጥረው በጀመሩት አጋማሽ የሀዋሳ ከተማን የተከላካይ መስመር ለመፈተን ጥረቶች አድርገዋል ።

በአጋማሹ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይም ጋዲሳ መብራቴ እና ቻርለስ ሙሴጌ ከሳጥን ውጪ ያደረጓቸው የግብ ሙከራዎች በግብ ጠባቂው መሀመድ ሙንታሪ በቀላሉ ተይዘዋል ።

የጨዋታው ደቂቃ 71 ላይ በደረሰበት ወቅት በጨዋታው እጅግ ለቀረበው የግብ ሙከራ የታየበት ነበር ። በአጋጣሚው ቻርለስ ሙሴጌ ለዳዊት እስጢፋኖስ ያቀበለውን ኳስ ዳዊት ከግቡ አናት በላይ ልኮታል ።

በአጋማሹ ተቀዛቅዘው የታዩት ሀይቆቹ በአዲሱ አቱላ እና አሊ ሱሌማን ካደረጓቸው ኢላሚቸውን ካልጠበቁ ኳሶች በቀር ጠንካራ የግብ ሙከራ ማድረግ አልቻሉም ።

በ78ኛው ደቂቃ ላይ ድሬዳዋ ከተማዎችን ጥረት ፍሬ አፍርቷል ። ኤልያስ አህመድ በሀዋሳ ከተማ የግራ መስመር አቅጣጫ በሚገኘው የሳጥኑ ክፍል ይዞ የገባውን ኳስ ከበረኛው ላይ ከፍ አድርጎ በማሳለፍ ለአቤል ከበደ የደረሰው ኳስ ድሬደዋ ከተማን መሪ አድርጓል ።

በቀጣዮቹ የጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ኳስ እና መረብን ለማገናኘት የነበሩት ጥረቶች ደካማ መሆንም ሙሉ የጨዋታውን ክፍለ ጊዜ በድሬዳዋ ከተማ 1 – 0 አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ አድርጓል ።

ውጤቱንም ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ ነጥቡን 27 በማድረስ ወደ 9ኛ ደረጃ ከፍ ሲል ሀዋሳ ከተማ በበኩሉ በ31 ነጥብ በነበረበት የአራተኛ ደረጃ ለመቆየት ተገዷል ።

በ21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ረቡዕ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ ሀዋሳ ከተማ ፋሲል ከተማን ሲገጥም ከሁለት ቀናት በኋላ በዕለተ አርብ ከቀን 9:00 ጀምሮ ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን የሚገጥም ይሆናል ።

You Might Also Like

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….

“ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ ወሳኙን ጨዋታ በድል ተወጥተዋል !!
Next Article አትሌት ሲፋን ሀሰን በለንደን ማራቶን አሸንፋለች

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

ሀትሪክ ስፖርት በማክሰኞ እትሟ ባለቀለሟ፣ ሳምንታዊዋ እና ዘወትር ማክሰኞ ለንባብ የምትበቃው ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገም የተለያዩ የሀገር ውስጥና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛ ለመውጣት ተዘጋጅታለች፡፡

hatricksport team By hatricksport team 4 years ago
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ
በ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ላይ ውሳኔዎች ተላለፉ !
ወልድያ ስፖርት ክለብ  በ 3 ተጨዋቾቹ ላይ  ከፍተኛ የቅጣት ውሳኔ አሳለፈ፡፡
የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ምድብ ድልድል ይፋ ሆኗል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?