መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ ሀዋሳ ከተማን አሸንፏል
ሀዋሳ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየጨዋታ ዘገባድሬዳዋ ከተማ

የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ ሀዋሳ ከተማን አሸንፏል

አጋራ
አጋራ

በሊጉ የ20ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ሀዋሳ ከተማን አሸንፏል ።

በድሬዳዋ ከተማ በኩል በ19ኛው ሳምንት በባህርዳር ከተማ በተረቱበት ጨዋታ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አምስት ለውጦችን አድርገው ገብተዋል ። አሳንቴ ጎድፍሬድ ፣ አሰጋኸኝ ጴጥሮስ ፣ ብሩክ ቃልቦሬ ፣ አቤል አሰበ እና ሄኖክ ሀሰን ምትክ
መሳይ ጳውሎስ ፣ እንየው ካሳሁን ፣ ዮሴፍ ዮሀንስ ፣ ዳዊት እስጢፋኖስ እና ጋዲሳ መብራቴ በመጀመሪያው አሰላለፍ ተካተዋል ።

በሀዋሳ ከተማ በኩል ደግሞ ወልቂጤ ከተማን ከረቱበት ጨዋታ ሶስት ለውጦችን በማድረግ በመድኃኔ ብርሀኔ ፣ አዲሱ አቱላ እና ሙጂብ ቃሲም ምትክ አብዱልባሲጥ ከማል ፣ ዳንኤል ደርቤ እና እዮብ አለማየሁ በምርጥ 11 አካተዋል ።


ቀዝቀዝ ባለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የጀመረው ጨዋታ በአንፃራዊነት ሀዋሳ ከተማዎች የተሻሉ ሆነው የታዩበት ነበር ።

ድሬዳዋ ከተማዎች በተወሰኑ አጋጣሚዎች ወደ ፊት ለመድረስ ጥረት ከማድረጋቸው ውጪ ይህ ነው ሊባል የሚችል ዕድል አልፈጠሩም ።

በሀዋሳ ከተማ በኩል ሁነኛ የፊት አጥቂያቸው ሙጂብ ቃሲም አለመኖር በተወሰኑ መልኩ በማጥቃት ላይ ክፍተት እንደፈጠረባቸው ማሳያዎች ነበሩ ።

በጨዋታው ቀዳሚ የግብ ሙከራ በ17ኛው ደቂቃ ላይ የተደረገ ሲሆን አሊ ሱሌማን የድሬዳዋ ከተማ ተከላካዮችን አልፎ ኳስ እና መረብን ለማገናኘት ያደረገው ጥረት ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል ።

ከአስር ደቂቃዎች በኋላም ኤርትራዊው አጥቂ አሊ ሱሌማን ከበቃሉ ገነነ የደረሰውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቶበታል ።

የመጀመሪያው አጋማሽን ግብ ሳይቆጠርበት 0 – 0 ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የተሻሉ ሆነው የታዩት ደግሞ ድሬዳዋ ከተማዎች ነበሩ ። ብርቱካናማዎቹ የተሻለ ጫና ፈጥረው በጀመሩት አጋማሽ የሀዋሳ ከተማን የተከላካይ መስመር ለመፈተን ጥረቶች አድርገዋል ።

በአጋማሹ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይም ጋዲሳ መብራቴ እና ቻርለስ ሙሴጌ ከሳጥን ውጪ ያደረጓቸው የግብ ሙከራዎች በግብ ጠባቂው መሀመድ ሙንታሪ በቀላሉ ተይዘዋል ።

የጨዋታው ደቂቃ 71 ላይ በደረሰበት ወቅት በጨዋታው እጅግ ለቀረበው የግብ ሙከራ የታየበት ነበር ። በአጋጣሚው ቻርለስ ሙሴጌ ለዳዊት እስጢፋኖስ ያቀበለውን ኳስ ዳዊት ከግቡ አናት በላይ ልኮታል ።

በአጋማሹ ተቀዛቅዘው የታዩት ሀይቆቹ በአዲሱ አቱላ እና አሊ ሱሌማን ካደረጓቸው ኢላሚቸውን ካልጠበቁ ኳሶች በቀር ጠንካራ የግብ ሙከራ ማድረግ አልቻሉም ።

በ78ኛው ደቂቃ ላይ ድሬዳዋ ከተማዎችን ጥረት ፍሬ አፍርቷል ። ኤልያስ አህመድ በሀዋሳ ከተማ የግራ መስመር አቅጣጫ በሚገኘው የሳጥኑ ክፍል ይዞ የገባውን ኳስ ከበረኛው ላይ ከፍ አድርጎ በማሳለፍ ለአቤል ከበደ የደረሰው ኳስ ድሬደዋ ከተማን መሪ አድርጓል ።

በቀጣዮቹ የጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ኳስ እና መረብን ለማገናኘት የነበሩት ጥረቶች ደካማ መሆንም ሙሉ የጨዋታውን ክፍለ ጊዜ በድሬዳዋ ከተማ 1 – 0 አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ አድርጓል ።

ውጤቱንም ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ ነጥቡን 27 በማድረስ ወደ 9ኛ ደረጃ ከፍ ሲል ሀዋሳ ከተማ በበኩሉ በ31 ነጥብ በነበረበት የአራተኛ ደረጃ ለመቆየት ተገዷል ።

በ21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ረቡዕ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ ሀዋሳ ከተማ ፋሲል ከተማን ሲገጥም ከሁለት ቀናት በኋላ በዕለተ አርብ ከቀን 9:00 ጀምሮ ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን የሚገጥም ይሆናል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...