By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ቡናማዎቹ ወደ አሸናፊነት ተመልሰዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካውንት ታገደ
አትሌቲክስ ዜናዎች
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮ-ኤሌክትሪክኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ቡናማዎቹ ወደ አሸናፊነት ተመልሰዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 7 months ago
Share
SHARE

በ24ተኛዉ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ዕለት ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና በወራጅ ቀጠናዉ ላይ የሚገኘዉን ኢትዮ ኤሌክትሪክ 1ለ0 በሆነ ጠባብ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በደረጃ ሰንጠረዡ ወገብ ዘጠነኛ ላይ የተቀመጠዉ የአሰልጣኝ ዮሴፍ ተስፋዬው ኢትዮጵያ ቡና እና በወራጅ ቀጠናው አስራ አምስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠዉ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ባደረጉት የዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታም ሁለቱም ክለቦች በሜዳዉ የመሐል ክፍል ላይ የተሻለ ለመንቀሳቀስ የሞከሩ ቢሆንም በሙከራ ረገድ ግን ቡናማዎቹ የተሻሉ ሁነዉ ተስተውሏል።

በዚህም ጨዋታዉ ከጀመረበት ደቂቃ አንስቶ ብልጫ መውሰድ የቻሉት ቡናማዎቹ በ12ተኛዉ ደቂቃ ላይ በወጣቱ የቀኝ መስመር ተመላላሽ ቃልአብ አማካኝነት ጥሩ የግብ ዕድል መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ተከላካዩ ተስፋ በቀለ መልሶበታል። ከስድስት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ ከግብ ጠባቂዉ የተሻገረለትን ኳስ አጥቂዉ መሐመድኑር ናስር ከኤሌትሪክ ተከላካዮች ጋር ታግሎ ሞከሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ በግቡ አናት ላይ ወጥታለች።

- ማሰታውቂያ -

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም የተሻለ ብልጫ መውሰድ የቻለዉ ኢትዮጵያ ቡና በ35ተኛዉ ደቂቃ ግብ ለማሰቆጠር ተቃርቦ ነበር ፤ በዚህም አጥቂዉ ጫላ ተሽታ ለአማኑኤል ያቀበለዉን ኳስ  መሐመድኑር ቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት ወደ ውጭ ወጥታለች።

ጥሩ ጥሩ የሚባሉ የግብ ዕድሎችን ማግኘት የቻለዉ ጫላ በ34ተኛዉ ደቂቃ አስቆጪ የሚባል ሙከራን ካደረገ ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ በድጋሚ ጫላ ተሽታ ከሮቤል የተሻገረለትን ኳስ በጭንቅላቱ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ኢላማዋን ሳትጠብቅ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በመጀመሪያው ኢጋማሽ ይህ ነዉ የሚባል ተጠቃሽ ሙከራ ለማድረግ ሲቸገር የተስተዋለው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በአጋማሹ በአብዛኛው ሀይልን የቀላቀለ የጨዋታ መንገድ እና አልፎ አልፎ በሚገኙ አጋጣሚዎች ደግሞ በመልሶ ማጥቃት ወደ ቡና የግብ ክልል ለመድረስ ሲጥሩ ተስተውሏል።

ከዕረፍት መልስ መልስ ሁለቱም ቡድኖች ተሻሽለዉ ወደ ሜዳ ሲመለሱ በ54ተኛዉ ደቂቃ ላይም ቡናማዎቹ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ በዚህም የኤሌትሪኩ የመሐል ተከላካይ ተስፋየ በቀለ ሳጥን ውስጥ ኳስን በእጁ መንካቱን ተከትሎ የተሰጠውን ፍፁም ቅጣት ምት ሮቤል ተክለሚካኤል ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ከዚች ግብ መቆጠር በኋላ በሙከራ ረገድ እምብዛም ባልነበረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ቡናማዎቹ በመሐመድኑር እና እነተነህ ተፈራ አማካኝነት ሙከራዎችን ቢያደርጉም ተጨማሪ ግብ ግን ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።

እንደ መጀመሪያው አጋማሽ ሁሉ በሁለተኛዉ አጋማሽም ሙከራዎችን ለማድረግ ሲቸገሩ የተስተዋሉት ኤሌትሪኮች በ77ተኛዉ ደቂቃ ላይ አማካዩ አብነት ደምሴ ከሳጥን ውጭ ካደረገዉ ሙከራ ውጭ በሙሉ ዘጠና ደቂቃ አንድም ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ማድረግ ሳይችሉ ቀርተዉ በኢትዮጵያ ቡና 1ለ0 በሆነ ዉጤት ተሸንፈዋል።

ዉጤቱን ተከትሎም ድል የቀናዉ ኢትዮጵያ ቡና በ34 ነጥብ ወደ አራተኛ ደረጃ ከፍ ማለት ሲችል ፤ በተቃራኒው ኤሌክትሪክ በ11 ነጥቦች አስራ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

You Might Also Like

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካውንት ታገደ

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ መድኅንን የረታበት ጨዋታ ውጤት በጊዜያዊነት እንዳይፀድቅ ተወሰነ
Next Article የጨዋታ ዘገባ | የአደም አባስ ብቸኛ ግብ የጣና ሞገዶቹን አሸናፊ አድርጓል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችየዝውውር ዜናዎችፋሲል ከተማ

የዝውውር ዜና ፋሲል ከተማ ኬኒያዊውን ሁለገብ ተጨዋች ሰንደይ ሙቱኩን አስፈረመ

የሻነው ግዛቸው By የሻነው ግዛቸው 6 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ቡናማዎቹ የጦና ንቦቹን ረተዋል
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሌላ የአቋም መለኪያ ጨዋታ እንደማያደርግ ተረጋግጧል
“ወልዋሎን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳለፋችን፤ ከመቀሌ ከተማም በላይ ሆነን በመቀመጣችን ተደስተናል”አላማንታ (ማሪዮ)
ጉዳፍ ፀጋይ የ1500 ሜትር የአለም ክብረወሰንን ስታሻሽል ሌሎች አትሌቶችም ድል ቀንቷቸዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?