By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ |የካርሎስ ዳምጠዉ ሁለት ጎሎች ለገጣፎ ለገዳዲን ባለድል አድርገዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሀዋሳ ከተማለገጣፎ ለገዳዲቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ |የካርሎስ ዳምጠዉ ሁለት ጎሎች ለገጣፎ ለገዳዲን ባለድል አድርገዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 1 year ago
Share
SHARE

 

በአሰልጣኝ ጥላሁን ተሾመ እየተመሩ በታሪካቸዉ ለመጀመሪያ ጊዜ በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳትፎን ማድረግ የቻሉት ለገጣፎ ለገዳዲዎች የመጀመሪያ ጨዋታቸዉን በድል ተወጥተዋል።

በዋና ዳኛ ተካልኝ ለማ ፊሽካ የተጀመረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ የመጀመሪያዎቹን አስራአምስት ደቂቃዎች ያህል ተመጣጣኝ ፉክክር ተመልክተንበታል ማለት ይቻላል። በተለይ የጨዋታው ሰዓት እየገፋ በመጣ ቁጥር ወደ ሪትማቸዉ በመግባት ጥሩ መንቀሳቀስ የቻሉት ክትፎዎቹ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ማድረግ ችለዉም ነበር ፤ በዚህም በተለይ ከቀኝ መስመር በኩል የተገኘዉን ቅጣተ ምት ዳንኤል ደርቤ ሲያሻማዉ ግዙፉ አጥቂ ሙጅብ ቃሲም ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም በግብ ዘቡ ወንደሰን አማካኝነት ኳሷ ወጥታለች።

በጨዋታዉ መባቻ ደቂቃ ላይ እንደ ቡድን ጥሩ የነበሩት ለገጣፎዎች ቀስ በቀስ በሀይቆቹ ብልጫ ሊወሰድባቸዉ ችሏል። በዚህም በተለይ በ26ኛዉ ደቀቃ ላይ አዲሱ አቱላ ያሻገረለትን ኳስ ኤርትራዊዉ አጥቂ አሊ ሱለይማን ወደ ግብነት ቀይሮ ሀይቆቹን መሪ ማድረግ ችሏል።

- ማሰታውቂያ -

ከግቧ መቆጠር በኋላ በይበልጥ የጨዋታ ብልጫ መዉሰድ ችለዉ የነበሩት ሀዋሳ ከተማዎች በ31ኛዉ ደቂቃ ላይ በድጋሚ ግብ ለማስቆጠር ከጫፍ ደርሰዉ ነበር ፤ በዚሁ ደቂቃ ላይም የመስመር ተከላካዩ ዳንኤል ደርቤ ያሻገረለትን ኳስ ኤፍሬም አሻሞ ቢያገኛትም አምክኗታል። ከዚህ ሙከራ በኋላም አጥቂው አሊ ሱለይማን በድጋሚ ግብ ለማስቆጠር ተቃርቦ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካለት ቀርቷል።

የጨዋታው የደት እየገፋ በመጣ ቁጥር መቀዛቀዝ ይታይባቸዉ የነበሩት ለገጣፎዎች የመጀመሪያው አጋማሽ ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች በቀሩበት ወቅት ግን አቻ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም በ42ኛዉ ደቂቃ ላይ ኪሩቤል ያሻማዉን ኳስ አጥቂዉ ካርሎስ ዳምጠዉ በግምባሩ በመግጨት ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል። በዚህም የመጀመሪያው አጋማሽ አንድ እኩል በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።

ከዕረፍት መልስ ሀይቆቹ በአጥቂያቸዉ አሊ ሱለይማን እና ሙጅብ ቃሲም በተደጋጋሚ የግብ ሙከራ ማድረግ ሲችሉ ፤ በተቃራኒው ለገጣፎዎች የፊት መስመር አጥቂያቸዉን ካርሎስ ዳምጠዉን መሰረት ያደረጉ ረጃጅም ኳሶችን በመላክ ከጨዋታዉ አንዳች ነገርን ለመፍጠር ሲታትሩ ተስተውሏል። በዚህም ጣፎዎች ዉጥናቸዉ ሰምሮ በ61ኛዉ ደቂቃ ላይ የሀዋሳ ከተማዉ ተከላካይ ላዉረንስ ላርቴ ኳሷን በግንባሩ ለግብ ጠባቂዉ መሀመድ ሙንታሪ ለማቀበል ሲጥር ግዙፉ አጥቂ በመሀል ደርሶ ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር ለገጣፎን መሪ ማድረግ ችሏል።

ከግቧ መቆጠር በኋላ በዕለቱ ድንቅ ሲንቀሳቀስ የነበረዉ አጥቂዉ ካርሎስ ዳምጠዉ ለራሱም ለክለቡም ሶስተኛ ግብ ለማስቆጠር የሚችልበትን ተደጋጋሚ ዕድል አግኝቶ የነበረ ቢሆንም ሳይጠቀምባቸዉ ቀርቷል። በአንፃሩ በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ጥሩ ሲንቀሳቀሱ እና መሪ መሆን ችለዉ የነበሩት ሀይቆቹ የኋላ ኋላ በተቆጠሩባቸዉ ግቦች ቢመሩም አቻ ለመሆን በሁሉም ረገድ ሲጥሩ የነበረ ቢሆንም በጨዋታዉ ተጨማሪ ግብ ማግኘት ሳይችሉ ቀርተዉ በአዲስ አዳጊዉ ለገጣፎ ለገዳዲ 2ለ1 በሆነ ዉጤት ተሸንፈዋል።

በቀጣይ ለገጣፎ ለገዳዲ ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ሲገናኙ በተመሳሳይ ሀዋሳ ከተማ ደግሞ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የድቻ እና ኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ ያለግብ አቻ ተጠናቋል
Next Article የጨዋታ ዘገባ |የምንይሉ ወንድሙ ብቸኛ ግብ መቻልን ባለድል አድርጋለች !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየኮከብ ተጫዋቾች ምርጫ

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ለምርጥ 10 ተጫዋቾች ምርጫ 32 ዕጩዎች ታውቀዋል

Mussie Girmay By Mussie Girmay 5 years ago
ሪፖርት | የሊጉ መሪ ደደቢት በባለሜዳው ወላይታ ድቻ ሽንፈት አስተናግዷል
ወላይታ ድቻ ዘላለም ሽፈራውን አዲስ አሰልጣኝ አድርጎ ቀጠረ
THE BIG INTERVIEW WITH : AYNALEM HAILE ||“በሄድኩበት ቦታ ተጨዋቾቹ ሳይቀር ወደ ዘረኝነት መሄዳቸው ያሳስበኛል” የፋሲሉ አይናለም ኃይለ (ገብርዬ)
ፋሲል ከነማና ጅማ አባ ቡና ድል ቀንቷቸዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?