By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ፈረሰኞቹ በአዳማ ከተማ ሽንፈት ሲያስተናግዱ ፤ ሀድያ ሆሳዕና ሀምበሪቾ ዱራሜን ማሸነፍ ችሏል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስአዳማ ከተማሀምበሪቾ ድራሜሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በአዳማ ከተማ ሽንፈት ሲያስተናግዱ ፤ ሀድያ ሆሳዕና ሀምበሪቾ ዱራሜን ማሸነፍ ችሏል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

ቀን 10:00 ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ መሪነት በተጀመረዉ የዕለቱ ቀዳሚ መርሐግብር ገና በመባቻዉ በሙሴ ኪሮስ አማካኝነት ሙከራ አድርገው በግብ ዘቡ ባህሩ ነጋሽ አማካኝነት ኳሱ የወጣባቸዉ አዳማዎች በ6ተኛዉ ደቂቃ ላይ መሪ መሆን ችለዋል። በዚህም ከግራ በኩል ዮሴፍ ታረቀኝ ያሻማዉን ኳስ ሙሴ ኪሮስ ወደ ግብነት ቀይሮ አዳማ ገና በመባቸዉ ጨዋታውን መምራት ጀምሯል።

ገና ከጅምሩ ግብ ያስተናገዱት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸዉን ግብ ለማስቆጠር በተደጋጋሚ ጫና ፈጥረዉ በመጫወት ሙከራዎችን ሲያደርጉ ፤ ለአብነትም በሁለቱም ኮሪደሮች በኩል የተሻሙ ኳሶችን ሞሰስ ኦዶ እና በረከት ወልዴ ወደ ግብ ሞክረዉ የነበረ ቢሆንም ኳሶቹ ኢላማቸዉን ሳይጠብቁ ቀርተዋል።

በ33ተኛዉ ደቂቃ ላይ ቦና አሊ የፈረሰኞቹ ተከላካዮች የሰሩትን ስህተት ተከትሎ ያገኘዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት በግቡ አግዳሚ ወጥታለች። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ መርሐግብር አጋማሹ ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩ አማኑኤል ኤርቦ ከናትናኤል ዘለቀ እና ሄኖክ ባገኛቸዉ ኳሶች ግብ ለማስቆጠር ተቃርቦ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ ሰይድ ሀብታሙ ኳሶቹን አምክኗቸዋል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስም 54ተኛዉ ደቂቃ ላይ አዳማ ከተማዎች ሁለተኛ ግብ አግኝተዋል። በዚህም በመልሶ ማጥቃት የተገኘዉን ኳስ ቢነያም አይተን ከዮሴፍ ታረቀኝ ጋር በአንድ ሁለት ቅብብል ቢኒያም ሳጥን ከገባ በኋላ ግብ ጠባቂዉን ባህሩ ጭምር አታሎ በማለፍ ሁለተኛ ግብ ለአዳማ ማስቆጠር ችሏል።

ምንም እንኳን ግብ አያስቆጥሩ እንጅ በኳስ ቁጥጥሩ የተሻሉ የነበሩት ፈረሰኞቹ በተደጋጋሚ ወደ ሶስተኛዉ የሜዳ ክፍል የሚደርሱ ሲሆን በ70ኛዉ ደቂቃ ላይ በረከት ወልዴ ከርቀት ሙከራ ማድረግ ችሎ ነበር ፤ በ77ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን ጊዮርጊስ ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸዉን ግብ አግኝተዋል ፤ በዚህም በግራ በኩል ረመዳን የሱፍ ከተገኑ የተቀበለዉን ኳስ ለእያሱ አቀብሎት ተጫዋቹ ኳሷን ወደ ግብነት መቀየር ችሏል። በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ተቀዛቅዞ የቀጠለዉ የቀን አስር ሰዓት ጨዋታም በአዳማ ከተማ 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

* በሊጉ በርካታ የአቻ ዉጤቶችን በማስመዝገብ ቀዳሚዉ የሆነዉ ሀድያ ሆሳዕና ሀምበሪቾ ዱራሜን 2ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

ምሽት አንድ ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ አማካኝነት ፊሽካ በጀመረዉ የምሽቱ ጨዋታ ገና በጅምሩ በተከታታይ ጨዋታዎችን ማሸነፍ ያልቻሉት ሀድያዎች በአጥቂዉ ዳዋ ሆቴሳ አማካኝነት ጥሩ የግብ ሙከራ ማድረግ ችለዋል። በተመሳሳይ እንደ ተጋጣሚያቸው ሁሉ ገና በጅምሩ ሙከራ ማድረግ የጀመሩት ሀምበሪቾዎች በ7ተኛዉ ደቂቃ ላይ በዳግም በቀለ አማካኝነት ከርቀት ድንቅ ሙከራ ቢያደርጉም የግብ ዘቡ ፔፔ አልዛየር ኳሷን ተቆጣጥሯል።

በዚህ ሂደት ጀምሮ በተመጣጣኝ እንቅስቃሴ በቀጠለዉ የምሽቱ መርሐግብር ከመሐል ሜዳዉ የኳስ ቅብብል የዘለለ ይህ ነዉ የሚባል ተጠቃሽ ሙከራ ሳይደረግበት አጋማሹ ያለ ግብ ተጠናቋል። ከዕረፍት መልስ በጥሩ ንቃት ጨዋታዉን የጀመሩት ሀድያዎች በ53ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከቀኝ በኩል ሳሙኤል ዮሐንስ ያሻማዉን ኳስ ዳዋ ሆቴሳ በግንባሩ በመግጨት ወደ ግብ ቢሞክርም ኳሷ የግቡን አግዳሚ ነክታ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በግራ መስመር በኩል በምሽቱ ጥሩ በመንቀሳቀስ የተጋጣሚዉን ቡድን የተከላካይ ክፍል ሲረብሽ ያመሸዉ ዳዋ ሁቴሳ ከግራ በኩል ጥሩ ኳስ ለተመስገን ብርሀኑ አቀብሎት ተጫዋቹ በግሩም ብቃት ኳሷን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ ምላሽ ለመስጠት መንቀሳቀስ የጀመሩት ሀምበሪቾዎች በ72ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከቅጣት ምት በዳግም በቀለ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ቢያደርጉም ኳሷ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በድጋሚ በ78ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሀምበሪቾዎች የአቻነት ግብ ለማግኘት ተቃርበዉ የነበረ ቢሆንም የመሀል ተከላካዩ ቃልዓብ ዉብሸት በሚገርም ሁኔታ ከልክሏቸዋል። መደበኛዉ ዘጠና ደቂቃ ሊጠናቀቅ 3 ደቂቃ ሲቀር ግን ነብሮቹ ሁለተኛ ግብ አክለዋል ፤ በዚህም ከኋላ ክፍል የተጣለዉን ኳስ ዳዋ ሆቴሳ በጥሩ ቅልጥፍና ኳሱን ከተቆጣጠረ በኋላ ኳሱን ገፍቶ አንድ ለአንድ ከግብ ጠባቂዉ ጋር ከተገናኘ በኋላ ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር ለክለቡ ሁለተኛ ግብ አስቆጥሮ መርሐግብሩ በሀድያ 2ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የኢትዮጵያ ቡና የቤተሰብ ሩጫ የ2 ሚሊዮን ብር ስፖንሰር አገኘ…
Next Article ሀዋሳ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎች

የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ሊዘጋ 180 ደቂቃዎች ቀርተውታል….

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 3 years ago
የእግር ኳሱን መንደር ሲያምሱት የነበሩት አቶ ተኽለወይኒ አሰፋ በአፍ ወለምታ የትግራይ ውክልናን አጡ፤የእሳቸው ውክልና መነሳት ለእግር ኳሱ መንደር ትልቅ ኦፎይታን ፈጥሯል
​የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ5 አመት የሚቆይ የሰላሳ ሚሊዮን ብር የስፖንሰርሺፕ.ስምምነት ተፈራረመ 
ቢንያም በላይ በኣልባኒያ ሊግ የመጀመርያ ጎሉን ኣስቆጠረ
ቅዱስ ጊዮርጊስ አራት ተጫዋቾችን ከተስፋ ቡድን ወደ ዋናው ቡድን አሳደገ።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?