የጣና ሞገዶቹ ሶስቱ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቾች ባስቆጠሩት ግብ ተጋጣሚያቸዉን ኢትዮጵያ ቡና 3ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል ።
ቀን 10 ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ማኑሄ ወልደፃዲቅ ፊሽካ በጀመረዉ የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ቡናማዎቹ ገና በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ምንም እንኳን በመሐል ሜዳዉ ላይ ብልጫ ይወስድባቸዉ እንጅ በተደጋጋሚ ወደ መስመር ባዘነበሉ እንቅሰቃሴዎች የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ ተስተውሏል።
በዚህም በና በመባቻዉ አንተነህ ተፈራ ከቀኝ የቡና ማጥቃት በኩል በቀጥታ ለመስፍን ታፈሰ ያሻገረዉን ኳስ በግራ መስመር በኩል የሚገኘዉ ተጫዋቹ ኳሷን ሳይቆጣጠራት የቀረባት መንገድ በቡናማዎቹ በኩል የመጀመሪያዋ አስቆጪ አጋጣሚ ነበረች ።
- ማሰታውቂያ -
በተቃራኒዉ ጥሩ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ እያስመለከቱን የነበሩት ባህርዳሮች በ23ተኛዉ ደቂቃ ላይ የመጀመሪያ ሙከራዎችን አድርገዋል ፤ በዚህም በቀኝ በኩል ተከላካዩ መሳይ አገኘሁ ከአማካዩ ፍሬዉ የተቀበለዉን ኳስ ከሳጥኑ ዉጭ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ በረከት ኳሷን ሲመልሳት ፤ በ35ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን ግብ አግኝተዋል በዚህም አማካዩ የአብስራ ከአብዱልከሪም ወርቁ የቀማዉን ኳስ ከግራ መስመር በኩል ለአጥቂዉ ሙጅብ ቃሲም አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል ።
በዚህ ሂደት ቀጥሎ አጋማሹ ሊጠናቀቅ የዳኛዉ ፊሽካ ሲጠበቅ የጣና ሞገዶቹ ተጨማሪ ግብ አክለዋል ፤ በዚህም እንደመጀመሪያው ሁሉ ወንድሜነህ ደረጀ በስህተት ለሀብታሙ ታደሰ የሰጠዉን ኳስ ራሱ ተጫዋቹ በአስገራሚ ሁኔታ ከፍሬው ሰለሞን ጋር አንድ ሁለት ተቀባብሎ ወደ ግብነት በመቀየር አጋማሹ በባህርዳር ከተማ ሁለት ለዜሮ መሪነት ተጠናቋል።
ከዕረፍት መልስ አራት ተጫዋቾችን ቀይረዉ ወደ ሜዳ ያስገቡት ቡናማዎቹ በ53ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ አግኝተዋል ፤ በዚህም ከማዕዘን የተሻገረዉን ኳስ መስፈን በግንባሩ ሲገጨዉ ግብ ጠባቂዉ ሲመልሰዉ አጠገቡ የነበረዉ አንተነህ ኳሷን ወደ ግብነት ቀንሮ ቡድኑን ወደ ጨዋታ መልሷል።
ይበልጥኑ ጥንቃቄ ላይ ያመዘነ የጨዋታ እንቅስቃሴን የመረጡት የጣና ሞገዶቹ በ66ተኛዉ ደቂቃ ላይ በቸርነት ጉግሳ ድንቅ የግብ ሙከራ አድርገዉ የነበረ ሲሆን ፤ ከደቂቃዎች በኋላ በ72ተኛዉ ደቂቃ ግን ችርነት ጉግሳ ከፍሬዉ ሰለሞን የተቀበለዉን ኳስ በማስቆጠር የክለቡን መሪነት ወደ ሶስት ለአንድ ከፍ ማድረግ ችሏል።
የጨዋታዉ ደቂቃ እየገፋ በሄደ ቁጥር ወደ ፉክክር የሚመልሳቸዉን ግብ ለማግኘት ይታትሩ የነበሩት ቡናማዎቹ በ77ኛዉ ደቂቃ ላይ በአንተነህ ተፈራ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ አድርገዉ የግቡ ቋሚ መልሶባቸዉ ተጨማሪ ግብ በጨዋታው ሳይቆጠር መርሐግብሩ 3ለ1 በሆነ ዉጤት በባህርዳር ተከማ አሸናፊነት ተጠናቋል።
አዳማ ከተማ ሀምበሪቾ ዱራሜን ሶስት ለአንድ በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል ።
ምሽት አንድ ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ሙሉቀን ያረጋል መሪነት በጀመረው የምሽቱ መርሐግብር አዳማ ከተማዎች በመጠኑ ከተጋጣሚያቸው ተሽለዉ ተሽለዉ ቶሎ ቶሎ ወደ ሀምበሪቾ የግብ ክልል በመድረስ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን ፤ በሙከራ ረገድ ግን በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ሁለቱም ክለቦች ተቀዛቅዘዉ ተስተዉሏል ።
በዚህም በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ከነበሩት ሙከራዎች መካከል ፤ በ17ተኛዉ ደቂቃ ላይ ዮሴፍ ከፈለኝ ለቦና አሊ አቀብሎት ተጫዋቹ ኳሷን ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ወደ ዉጭ ወጥታለች ። ዳግም በ35ተኛዉ ደቂቃ ላይ በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ ቦና አሊ አስገራሚ ኳስ ለዮሴፍ ከፈለኝ አቀብሎት ተጫዋቹ ኳሷን ወደ ግብ ቢሞክራትም ኳሷ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች።
በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም አጋማሹ ሊገባደድ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩ አዳማ ከተማዎች መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ አስቆጥረዋል ፤ በዚህም ከኋላ ክፍል በረዥሙ የተሻገረዉን ኳስ የሀምበሪቾ ተከላካዮች ሲመልሱት ኳሷን ያገኘዉ ቦና አሊ በድንቅ ብቃት ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።
ከዕረፍት መልስ አሁንም እንደመጀመሪያው አጋማሽ ሁሉ ብልጫ የነበራቸዉ አዳማዎች በ51ኛዉ ደቂቃ ላይ መሪነታቸዉን ወደ ሁለት ለዜሮ ከፍ ማድረግ የቻሉበትን ግብ አግኝተዋል ። በዚህም በቀኝ መስመር በኩል ኳስ እየገፋ ሳጥን ዉስጥ የገባዉ ዮሴፍ ታረቀኝ ላይ የተሰራዉን ጥፋት ተከትሎ የተሰጠዉን ፔናሊቲ ቦና አሊ ወደ ግብነት በመቀየር የአዳማን መሪነት ወደ ሁለት ለዜሮ ከፍ አድርጓል።
ያን ያህል በጨዋታዉ ላይ አደጋ መፍጠር ያልቻሉት ሀምበሪቾዎች ተደጋጋሚ ሙከራዎች ከተደረጉባቸዉ በኋላ በ70ኛዉ ደቂቃ ላይ ሶስተኛ ግብ ተቆጥሮባቸዋል ፤ በዚህም ከፍቅሩ አለማየሁ የተቀበለዉን ኳስ አጥቂዉ ዮሴፍ ታረቀኝ በድንቅ ብቃት ወደ ግብነት በመቀየር የምሽቱን ተጠባቂ መርሐግብር አዳማ ከተማ 3ለ0 በሆነ ዉጤት እንዲያሸንፍ አድርጓል።