መነሻ ገጽ ለገጣፎ ለገዳዲ ለገጣፎ ለገዳዲ ሊግ ኩባንያው ላይ የሚያሰማው ተቃውሞ ቀጥሏል
ለገጣፎ ለገዳዲቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ለገጣፎ ለገዳዲ ሊግ ኩባንያው ላይ የሚያሰማው ተቃውሞ ቀጥሏል

አጋራ
አጋራ

” አወዳዳሪው አካል የሀገሪቱን እግርኳስ ህግ በሚጻረር መልኩ ያዘዋወርናቸውን ተጨዋቾች እንዳንጠቀም በማድረግ 6 ነጥብ አሳጥቶናል”
ለገጣፎ ለገዳዲ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ የሆነው ለገጣፎ ለገዳዲ ህገወጥ ድርጊት ፈጽሞብኛል በማለት በሊግ ኩባንያው ላይ የሚያሰማውን ተቃውሞ አጠናክሮ ቀጥሏል።

ክለቡ ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዛሬ በላከው ደብዳቤ ከሲዳማ ቡናና መቻል ጋር የነበረው ጨዋታ ውጤት ተሽሮ እንዲደገም ጠይቋል። “ከሲዳማ ቡና ጋር ከነበረው ጨዋታ በማስገደድ መብታችንን ጥሰው እንድንጫወት ተደርገናል ከመቻል ጋር በነበረውም ጨዋታ ቡድን መሪው የተጨዋቾችን ስም ዝርዝር ልኮ እያለ አይቻልም በማለት አምስት ህጋዊ ተጨዋቾች ብቻ ናቸው ያሉት በሚል ሌሎቹ ከመልበሻ ቤት እንዳይወጡ በማድረግ ፎርፌ እንዲሰጥ አድርገውብናል በአጠቃላይ
አወዳዳሪው አካል የሀገሪቱን እግርኳስ ህግ በሚጻረር መልኩ ያዘዋወርናቸውን ተጨዋቾች እንዳንጠቀም በማድረግ 6 ነጥብ አሳጥቶናል” ሲሉ ከሰዋል።

ክለቡ በአራት ዓበይት ጉዳዮች ላይ ባነጣጠረው ደብዳቤው ” አወዳዳሪ አካሉ ህግ በመጣስ ያጣነው የሁለቱ ጨዋታ ነጥብ እንዲታይልን ፤በተጨዋቾቻችን ላይ የደረሰው እንግልትና ሞራላዊ ጥሰት ታይቶ ካሳ እንዲደረግልን፤ አሰልጣኙና ቡድን መሪውን ለምን መብታችሁን ጠየቃችሁ ብለው ያስፈራሩትን እንዲያቆሙ፤ የክለቡ አመራሮች ደውለው ሲያናግሩ ቀና ምላሽ አለማግኘታቸው ታይቶ ህጋዊ ምላሽ እንዲሰጠን እንጠይቃለን” ሲል ፌዴሬሽነን ጠይቋል።

የክለቡ የደብዳቤ ማሳረጊያ በጠንካራ ቃላት የታጀበ ሲሆን “ከላይ የጠየቅነው ጥያቄ ምላሽ ካላገኘን በቀጣዩ ጨዋታ ላይ ለመገኘት እንቸገራለን” ሲል ላቀረበው የፍትህ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጠው አሳስቧል። ፌዴሬሽኑም እስካሁን የተጣሰውን መብታችንን እንዲያስከብርልን አወዳዳሪ አካሉም ከተመሳሳይ ድርጊቱ እንዲቆጠብ እንዲደረግልን አበክረን እንጠይቃለን” ሲል አሳስቧል።

በሊግ ኩባንያው የውድድር መርሃግብር መሠረት በ16ኛው ሳምንት መርሃግብር ለገጣፎ ለገዳዲ ከሀዋሳ ጋር የዛሬ ሳምንት ሰኞ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ እንደሚጫወቱ ታውቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...