በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እየተሳተፈ ያለውና የሊጉን ዋንጫ ካነሱ ክለቦች ተርታ ስሙ የሚጠራውን ጅማ አባጅፋርን ውጤታማ አላደረገም በሚል የክለቡ አመራሮች አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለን አግደዋል።
ክለቡ በላከው ደብዳቤ አሰልጣኙን በማገድ ለጊዜው በምክትል አሰልጣኙ እንዲመሩ ወስኗል። በክለቡ ውሳኔም መሠረት አሰልጣኙ እስከ ሰኔ 30/2014 ድረስ ያለው ደመወዙ እንደሚከፈለው ታውቋል።
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በ20 ጨዋታ 13 ነጥብና 16 የግብ ዕዳ ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ በ15ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ጅማ አባጅፋር በቀጣዩ አርብ ከባህርዳር ከተማ ጋር የሚጫወት ሲሆን ክለቡን ከወራጅ ቀጠና ለማውጣት ጊዜያዊውም ይሁን ቀጣዩ አሰልጣኝ ላይ የተጣለ ትልቅ የቤት ስራ ሆኗል።