By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ |ፈረሰኞቹ እና ክትፎዎቹ ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….
ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወልቂጤ ከተማዜናዎች

የጨዋታ ዘገባ |ፈረሰኞቹ እና ክትፎዎቹ ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 1 year ago
Share
SHARE

 

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ7ተኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ የተገናኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወልቂጤ ከተማ ጨዋታቸውን ሁለት አቻ በሆነ ዉጤት አጠናቀዋል።

በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ምንም እንኳን በሁሉም ረገድ የቅዱስ ጊዮርጊስን የበላይነት የተመለከትን ቢሆነም ቀዳሚዋን ሙከራ በማድረግ ግን የገብረ ክርስቶስ ቢራራዉ ቡድን ቀዳሚ ነበር ፤ በዚህም በ12ኛዉ ደቂቃ ላይ ከመሐል ክፍል የተሻገረለትን ኳስ ጌታነህ ከበደ በጥሩ ዕይታ ለኋላሸት ሰለሞን አቀብሎት የነበረ ቢሆንም ተጫዋቹ ከበረኛ ጋር ተገናኝቶ ኳሷን አምክኗታል።

በ34ኛዉ ደቂቃ ላይ አማካዩ ጋቶች ፓኖም ያቀበለዉን ኳስ የፊት መስመር አጥቂዉ ኢስማኤል ኦሮ አጎሮ ከቀኝ መስመር ወደ ሳጥኑ ሲያሻግር ጥሩ አቋቋም ላይ ይገኝ የነበረዉ የመስመር ተጫዋቹ አማኑኤል ገ/ሚካኤል ወደ ግብነት ቀይሮ ቡድኑን መሪ ማድረግ ችሏል። በድጋሚ በ37ኛዉ ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር በኩል ከሄንክ አዱኛ የተቀበለውን ኳስ አማኑኤል ገ/ሚካኤል በግራ ዕግሩ አክርሮ ወደ ግብ ቢመታም ኳሷ ኢላማዋን ሳትጠብቅ ለጥቂት ወደ ዉጬ ወጥታለች።

- ማሰታውቂያ -

በአጋማሹ መጠናቀቂያ ላይ ደግሞ ክትፎዎች ድንቅ ግብ የማግባት አጋጣሚ አግኝተዉ ነበር በዚህም ከመሐል ክፍል የተሻገረለትን ኳስ አጥቂዉ ጌታነህ ከበደ በጭንቅላት ሲሞክር ግብ ጠባቂዉ ቻርልስ በሚመልስበት ሰዓት በአቅራቢያው ይገኝ የነበረዉ አቡበከር ሳኒ በድጋሚ ሲሞክር የፈረሰኞቹ ተከላካዮች እንደምንም ኳሱን አዉጥተዉታል።

ከዕረፍት መልስ ፈረሰኞቹ የማጥቃት ሀይላቸዉን አጠናክረዉ ወደ ሜዳ ቢገቡም በ55ኛዉ ደቂቃ ላይ በክትፎዎች በኩል ለግብ የቀረበ ሙከራ ተመልክተንበታል። በዚህም ጌታነህ ከበደ ያሻማውን ኳስ የኋላሸት ሰለሞን በጭንቅላቱ ግጭቶ ቢሞክርም ግብ ጠባቂዉ ሲመልስ ተጨራርፋ የተገኘችዉን ኳስ አቡበከር ሳኒ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም የቅዱስ ጊዮርጊስ ተከላካዮች እንደምንም አዉጥተዉታል።

በ70ኛዉ ደቂቃ ላይ ክትፎዎቹ አቻ መሆን የቻሉበትን ግብ ማግኘት ችለዋል። በዚህም በዕለቱ ኳስን በዕግሩ በመጫወት ረገድ ደካማ የነበረዉ ግብ ጠባቂዉ ቻርልስ ሉክዋጎ በትክክል ያላራቃትን ሷስ አቡበከር ሳኒ አግኝቶ ግብ በማስቆጠር ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ አጥቂው ጌታነህ ከበደ ከቀኝ መስመር በኩል ያሻማውን ኳስ አቡበከር ሳኒ በጭንቅላቱ በመግጨት ለራሱም ለክለቡም ሁለተኛውን ግብ ማስቆጠር ችሏል።

የጨዋታው ሰዓት እየገፋ በመጣ ቁጥር የአቻነት ግብ ለማግኘት ሲጥሩ የነበሩት ፈረሰኞቹ በ90+2 ላይ የአቻነት ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም መሰረት የመስመር ተከላካዩ ሱለይማን አህመድ ያሻማውን ኳስ ኢስማኤል ኦሮ አጎሮ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል። በዚህም የ6ተኛዉ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ሁለተኛ ጨዋታ 2አቻ በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።

You Might Also Like

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ይገዙ ቦጋለ ቅጣት ተጥሎበታል !!
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ መድን ሊጉን መምራት ጀምሯል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ባህርዳር ከተማዜናዎች

ባህርዳር ከተማ ግብ ጠባቂ አስፈርሟል

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 4 years ago
የጨዋታ ዘገባ | የአስረኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማን ባለ ድል አድርጓል
ዲያጎ ጋርዝያቶ አዲስ ክለብ ተረክበዋል !
ሶስት የዋልያዎቹ ተጫዋቾች ጉዳት አስተናግደዋል !
የወላይታ ድቻ ተጫዋቾች ቅሬታቸውን አሰምተዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?