አፄዎቹ በቀጣይ የዉድድር ዘመን በቀድሞዉ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዉበቱ አባተ እየተመሩ እንደሚሰለጥኑ ከተረጋገጠ በኋላ የተጫዋቾች ዝዉዉር ላይ የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ ፤ ቃልኪዳን ዘላለም የፋሲል የመጀመሪያ ፈራሚ መሆኑም ተረጋግጧል።
የቀድሞዉ የደደቢት እና የሰበታ ተጫዋች የነበረዉ እንዲሁም በዚህ የዉድድር አመት ለወላይታ ዲቻ ሲጫወት የነበረዉ ቃልኪዳን ዘላለም በሁለት አመት ኮንትራት ፋሲል ከነማን መቀላቀሉ እርግጥ ሆኗል፤ፋሲል ከነማ በቀጣይ ቀናትም ሌሎች ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ እንደሚቀላቅል ይጠበቃል።
ፋሲል ከነማ ከዝዉዉር በመታገዱ ምክንያት የተጫዋቹ ዉል በፌድሬሽን አልፀደቀም።