የኢትዮ ኤሌክትሪክ ቦርድ ከአሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ጋር ከተወያየ በኋላ ወደ ድሬዳዋ እንዲመለስና ከቡድኑ ጋር እንዲቆይ ወሰነ።
ትላንት አዲስ አበባ ገብቶ ዛሬ ከቦርዱ ጋር የተገናኘው አሰልጣኙ ቡድኑ ጋር ያለውን ጠንካራና ደካሜ ጎን ያስረዳ ሲሆን ቦርዱ ራሱ ውስጡን እንዲመረምር አንድ የደጋፊ ማህበሩ አመራርና አንድ የቦርድ አባል ቡድኑ ላይ የፈጠሩትን ችግርና ጫና በማስረዳት ያለውን እውነት ገልጿል
ቦርዱም በሰጠው ውሳኔ በአሰልጣኝ ክፍፍሌ የማይፈለገውን የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ መሃመድን ወደ ከ20 አመት በታች ቡድኑ እንዲመለስ፣ የቡድን መሪው አቶ በድሉ እና የህክምና ባለሙያዋ ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ አዟል።
አሰልጣኙ በቀጣይ ቡድኑን ወደ ውጤት እንዲመራ አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግለት ተነግሮት ወደ ድሬዳዋ እንዲመለስ በመወሰኑ በሶሰት አሰልጣኞች የተደረገው ስርሰራ መክሸፉ ታውቋል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ8ኛው ሳምንት መርሃግብር ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ግጥሚያውን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።