By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ” ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግብ አስቆጥሬ ደስታዬን እየገለጽኩ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎችን የማብሸቅበት ምክንያት የለም” “ምልክቱ ለፍቅረኛዬ ያለኝን ፍቅር ለመግለጽ ብቻ ነው …ሌላ ትርጉም የለውም ..” አዲስ ግደይ / ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ/
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ንግድ ባንክቃለመጠይቅ

” ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግብ አስቆጥሬ ደስታዬን እየገለጽኩ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎችን የማብሸቅበት ምክንያት የለም” “ምልክቱ ለፍቅረኛዬ ያለኝን ፍቅር ለመግለጽ ብቻ ነው …ሌላ ትርጉም የለውም ..” አዲስ ግደይ / ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ/

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
Share
SHARE

የቀድሞው የሲዳማ ቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ የአሁኑ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጨዋች የሆነው አዲስ ግደይ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግብ አስቆጥሮ ያሳየው ምልክት መነጋገሪያ ሆኗል… ተጨዋቹ የክለባችንን ምልክት ነው የዘቀዘቀው በማለት የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ሲቃወሙት ታይቷል ….በተገኘው ምክንያት መበሻሸቅ ልማዳቸው የሆነው የኢትዮጵያ ቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ጎራ ለይተው ሲነቋቆሩ ቢሰነብቱም ተጨዋቹ ግን ከሀትሪክ ድረገጹ ባልደረባ ዮሴፍ ከፈለኝ ጋር በነበረው ቆይታ ከደሙ ንጹህ ነኝ ብሏል….

ሀትሪክ:- አዲስ አመሰግናለሁ..ላሳየኧን ፈቃደኝነት..

አዲስ:- እኔም በጣም አመሰግናለሁ

ሀትሪክ :- እስቲ ስለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተሰላፊነትህ እናውራ…?

- ማሰታውቂያ -

አዲስ :- በታሪኬ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የተቀላቀልኩት …ክለቡም አዲስ አዳጊ ቡድን ነው አራት የሊግ ጨዋታዎችን አድርጌያለሁ ጥሩ የሚባል አጀማመር አድርገናል… አዲስ አዳጊ ይሁን እንጂ ሲኒየር ተጨዋቾችን ማካተቱ አጀማመሩን ጥሩ አድርጎታል በቀጣይም የተሻለ አቋም ይኖረዋል ብዬ አስባለሁ …አጀማመራችን ግን አሪፍ ነው….

ሀትሪክ:- ቅዱስ ጊዮርጊስን በጉዳት ለቀቀክ ..? ወይስ ..?

አዲስ:- በፍጹም …ይሄ በግልጽ መታወቅ አለበት በርግጥ ከሁለት አመት በፊት ጉዳት አጋጥሞኝ ነበር ከዚያ በኋላ በጥሩ ሁኔታ አገግሜ በጥሩ አካል ብቃትና ስነልቦና ወደ ውድድር ተመልሼ ጥሩ ልምምድ ስሰራ ቆይቻለሁ…በ2015 ግን በተለይ ከጥቅምት ጀምሮ በጥሩ ዝግጅት አሰልጣኞቼ የሚሰጡኝን ስልጠና በብቃት ስወጣ ቆይቼ ለጨዋታ ዝግጁ ብሆንም ግጥሚያ ማድረግ አልቻልኩም …. ብዙ የመሰለፍ እድል አላገኘሁም ለጨዋታው ግን ዝግጁ ነበርኩ የኔ ሃላፊነት ዝግጁ መሆን ነበር ዝግጁም ሆኜ አሰልጣኜ የሚለኝን ስሰራ ቆይቻለሁ የአሰልጣኙ ምርጫና ውሳኔ ሆኖ ብዙ ጨዋታ አልተሰለፍኩም እንጂ ሙሉ በሙሉ ጤነኛ እንደነበርኩ መታወቅ አለዘት..

ሀትሪክ:- ስለዚህ ንግድ ባንክ ጤነኛውና ባለልምዱን አዲስ ግደይን ነው ያገኘው ማለት ይቻላላ…?

አዲስ:- አዎ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የገባሁት በሙሉ ጤነኛ ሆኜ ራሴን ለማሳየት ለጨዋታው ዝግጁ ሆኜ ነው..

ሀትሪክ:- ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ምን ለማሳካት አቀድክ..?

አዲስ:- ዘንድሮ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የተቀላቀልኩት የቀድሞውን አዲስ ግደይን የመመለስ እቅድ ይዤ ነው .. አጀማመራችን ጥሩ ነው ከፍተኛ የሆነ በራስ መተማመን አለኝ ከረጅም ጊዜ በኋላ ጎል አስቆጥሬያለሁ…
ከቀድሞው አዲስ ግደይ የተሻለውን አዲስ ግደይን ይዤ እቀርባለሁ ጥሩ ጊዜ ይኖረኛል ብዬ አምናለሁ

ሀትሪክ :- ከሰሞኑ መነጋገሪያ የነበረው ጎል አስቆጥረህ ያሳየኧው ምልክት ነው …ጥቂት የማይባሉ ደጋፊዎች የኢትዮጵያ ቡና ምልክትን ዘቅዝቀህ አሳይተሃል ይሉሃል … ምን ምላሽ አለህ ..?

አዲስ :- የኢትዮጵያ ቡና ክለብ፣አባላትና ደጋፊዎችን ይቅርታ እጠይቃለሁ ይህን አይነት ቅሬታ በውስጣቸው ስለፈጠርኩ…ምናልባት ግን ምልክቱን ሳሳይ የሚያውቁኝ
ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስጫወት ነበር.. ነገር ግን ለሲዳማ ቡና ስጫወትና ግብ ሳስቆጥር ምልክቱን ሳሳየው ኖሬያለሁ.. …ማንም ግን ተናግሮኝ አያውቅም .. ቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ካላቸው የከተማ ተቀናቃኝነትና የደርቢ ስሜት አንጻር መበሻሸቂያ አድርገውት ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ.. የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በፎቶዬ ሲጠቀሙ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች እልህ ሊጋቡ እንደሚችሉ መገመት አያቅተኝም። ምልክቱ ግን ከኢትዮጵያ ቡና አርማ ጋር የሚሄድበት ምክንያት የለም ..ለሲዳማ ቡና ስጫወት ሶሻል ሚዲያው እንደ አሁኑ አልበረከተም… ትኩረትም አያገኝም…ከበፊት ጀምሬ በተለይ ከሲዳማ ቡና ተሰላፊነቴ ጀምሮ እንደማደርገው ማወቅ አለባቸው ለተፈጠረው ግን የኢትዮጵያ ቡና ደፊዎችን ይቅርታ እጠይቃለሁ።
.
ሀትሪክ :- የምታሳየው ምልክት ትርጉሙ ግን ምን ይሆን ….?

አዲስ :- ምልክቱን በተመለከተ ምክንያቱን ላልተረዱ ደጋፊዎች መናገር እፈልጋለሁ …. ለኢትዮጵያ ቡና ትልቅ ክብር አለኝ ይህን የሚያደርግ ሰብዕናም የለኝም… በጭራሽ አላደርግም.. በዋናነት ግብ አስቆጥሬ ማሳየትን የፈለኩት የፍቅረኛዬ ስም መነሻ ፊደል ነው ፊደሉ ኤም ሲሆን የፍቅረኛዬ ስም መነሻ ስለሆነ ፍቅሬን ለመግለጽ ነው….። የፍቅር ምልክቴ እንጂ ኢትዮጵያ ቡናን ለማንቋሸሽ ያደረኩት አይደለም የተከፉት ደጋፊዎች እንዲረዱኝ እጠይቃለሁ.. አሁን የምሰለፈው ማሊያውንም የማደርገው ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነው። ኢትዮጵያ ቡናን የማበሽቅበት ምክንያት የለም ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግብ አስቆጥሬ ደስታዬን ስገልጽ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎችን የማብሸቅበት ምክንያት የለም የኢትዮጵያ ቡናና የቅዱስጊዮርጊስ ደጋፊዎች ሲበሻሸቁ ስሜ ሊጠራ ይችላል ግን የኔ ሀሳብም አይደለም ይህን የሚፈጥር ህሊናም የለኝም

ሀትሪክ :-ለደጋፊዎቹ የመጨረሻ መልዕክት ካለህ..?

አዲስ :- ተቃውሞው ሰደበን ከሆነ ይቅርታ እጠይቃለሁ… ግን አልተሳደብኩም ነገ ለብሄራዊ ቡድን ስጫወት ግብ አስቆጥሬ ምልክቱን ባሳይ ብጨፍር ቅሬታ ሊነሳ ነው …? ለእኔ ግን አልተመቸኝም …ምልክቱ ለፍቅረኛዬ ያለኝን ፍቅር ለመግለጽ ብቻ ነው …ሌላ ትርጉም የለውም ..

ሀትሪክ:- አመሰግናለሁ..

አዲስ:- እኔም አመሰግናለሁ

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የሻሸመኔ ከተማ አሰልጣኝ ጸጋዬ ወንድሙ ራሱን ከአሰልጣኝነት አገለለ…
Next Article ”ከ15 ዓመት በኋላ በሊጉ ለሻሸመኔ ከተማ የመጀመሪያ ጎል ያስቀጠርኩ ታሪካዊ ተጫዋች በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል” ያሬድ ዳዊት/የሻሸመኔ ከተማ ተጫዋች/

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዋልያዎቹየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንአፍሪካዜናዎችአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ

የዋሊያዎቹ የጨዋታ ቀናት ተራዘሙ

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 4 years ago
የወልቂጤ ከተማ  9 ተጨዋቾች ልምምድ አቁመዋል
“የአቡበከር አስናደቂ አቋም አስደንግጦኛል፤ ኮከብነቱን በማግኘቱ አልከፋም” ሀብታሙ ተከስተ /ፋሲል ከነማ/
የሀድያ ሆሳዕና የፋይናንስ ሃላፊ ቅዳሜ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ
የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ መሪነታቸዉን አጠናክረው ቀጥለዋል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?