መነሻ ገጽ አፍሪካ ዋንጫ « ኢትዮጵያን በደርሶ መልስ አሸንፈን ስድስት ነጥብ እንወስዳለን » ካባ ዲያዋራ
አፍሪካ ዋንጫአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያዋልያዎቹዜናዎችጊኒ

« ኢትዮጵያን በደርሶ መልስ አሸንፈን ስድስት ነጥብ እንወስዳለን » ካባ ዲያዋራ

አጋራ
አጋራ

ለ2023 የኮት ዲቯር የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ በደርሶ መልስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን የሚገጥመው የጊኒ ብሐራዊ ቡድን አሰልጣኝ ካባ ዲያዋራ በሞሮኮ የሚደረጉትን ሁለት የደርሶ መልስ ጨዋታዎች አሸንፈው ሙሉ ስድስት ነጥብ እንደሚወስዱ ተናግረዋል፡፡

ማርች 24 እና ማርች 27 በሞሮኮ ከተሞች የሚደረጉትን ሁለት የደርሶ መልስ ጨዋታዎች አስመልክተው ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ ያደረጉት አሰልጣኝ ዲያዋራ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን በሚገባ እናውቀዋለን በምናውቃቸው መጠንም ተዘጋጅተናል ብለዋል፡፡

አሰልጣኙ ተጋጣሚያቸው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድንን አስመልክቶ ለተነሳላቸው ጥያቄ

« የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዘጠና በመቶ በላይ በሃገር ውስጥ ሊግ በሚጫወቱ ልጆች የተገነባ ብሔራዊ ቡድን ነው፤ የባለፈው የቻን ውድድር በደንብ እንድናያቸው ዕድል ፈጥሮልናል፣ ኳስ ይዘው መጫወት ይፈልጋሉ፣ ብዙ ይሮጣሉ፣ ሶስቱንም ጨዋታዎቻቸውን ተመልክተን ለነሱ የሚሆን ታክቲክ አዘጋጅተናል፤ ሁለቱንም ጨዋታዎች አሸንፈን ስድስት ነጥብ ከኢትዮጵያ ላይ ወስደን ወደኮት ዲቯር እናቀናለን፡፡»

የሁለቱ ሃገራት ጨዋታዎች በማርች 24 በካዛብላንካ መሃመድ አምስተኛ እንዲሁም የመልሱ ጨዋታ ደግሞ ማርች 27 በራባት ከተማ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ይደረጋሉ፡፡

ከሜዳቸው ውጪ መጫወታቸው በውጤቱ ላይ ልዩነት ይፈጥር እንደሆነ የተጠየቁት አሰልጣኙ ሲመልሱ

« ሞሮኮን የመረጡት ሁለቱም ፌዴሬሽኖች በስምምነት ነው፤ ወቅቱ የራማዳን ጾም ወቅት በመሆኑ ለኛም በመሃል ጉዞ ሳናደርግ መጫወታችን ይጠቅመናል የትራንስፖርት ወጪም ይቀንሳል፤ በርካታ ጊኔያውያን በሞሮኮ እንደሞኖራቸው በኛ ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖራል ብዬ አላስብም ዋናው ነገር በርካታ ጊኒያውያውያን በስታዲየም ተገኝተው ጨዋታውን እንዲመለከቱ መጋበዙ ላይ ነው፡፡»

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...