By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ባህርዳር ከተማ እና መቻል በተመሳሳይ ተጋጣሚዎቻቸዉን 1ለ0 በሆነ ዉጤት በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ይዘዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችባህርዳር ከተማመቻልሻሸመኔ ከተማ

ባህርዳር ከተማ እና መቻል በተመሳሳይ ተጋጣሚዎቻቸዉን 1ለ0 በሆነ ዉጤት በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ይዘዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ የጣና ሞገዶቹ ወላይታ ዲቻን 1ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል ።

ተመጣጣኝ የሚባል የሚባል የጨዋታ ፉክክር ባስመለከተዉ እና በተቃራኒው በሙከራ ረገድ ግን ደካማ በነበረዉ የዕለቱ ቀዳሚ መርሐግብር ባህርዳር ከተማዎች በይበልጥ በኳስ ቁጥጥር ተሽለዉ በመቅረብ አልፎ አልፎ የሚያገኟቸዉን ዕድሎች ወደ ግብነት ለመቀየር ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን ፤ በተቃራኒው ወላይታ ዲቻዎች ከኋላ መስመር የሚነሱ ኳሶችን ወደ ፊት በመጣል የጨዋታዉን የበላይነት ለመያዝ የሞከሩ ቢሆንም ነገር ግን ያን ያህል ተጠቃሽ ሙከራ ማድረግ ላይ እምብዛም ሆነዉ ተስተዉሏል ፤ በዚህም በመጀመሪያው አጋማሽ ዲቻዎች አብነት ደምሴ ባቀበለዉ ኳስ ቢኒያም ፍቅሬ ድንቅ ሙከራ አድርጎ ኳሷ ለጥቂት ወጥታለች።

በጨዋታዉ ረገድ የተሻሉ የነበሩት የጣና ሞገዶቹ በ31ኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም ከማዕዘን ምት የተሻገረዉን ኳስ የፊት መስመር ተጫዋቹ ቸርነት ጉግሳ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ከዕረፍት መልስ ወላይታ ዲቻዎች የአቻነት ግብ ፍለጋ በኳስ ቁጥጥሩ ተሽለዉ በተደጋጋሚ ወደ ፊት በመጠጋት ጫና ለመፍጠር ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን ፤ በተቃራኒው ባህርዳር ከተማዎች ደግሞ ያስቆጠሩትን ግብ አስጠብቀዉ ለመዉጣት ወደ ራሳቸዉ የግብ ክልል አፈግፍገዉ በመጫወት ተጨማሪ ግብ ሳይቆጠርባቸዉ 1ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል ።

- ማሰታውቂያ -

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ መቻል ሻሸመኔ ከተማን 1ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል ።

በተመጣጣኝ የሜዳ ላይ ፉክክር መከናወን በጀመረዉ የሁለት ክለቦች የአመሻሽ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ ጨዋታ ገና በመባቻዉ ግብ ተስተናግዶበታል ። በዚህም በ14ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሽመልስ በቀለ ያሻገረዉን ኳስ የሻሸመኔ ከተማ ተከላካዮች ሲመልሱት በቅርብ ርቀት ላይ የነበረዉ ከንዓን ማርክነህ በግሩም አጨራረስ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል ።

ግብ ካስቆጠሩ በኋላም በተደጋጋሚ የግብ ዕድሎችን በመፍጠሩ ረገድ የተሻሉ የነበሩት መቻሎች ዳግም ከሰባት ደቂቃዎች በኋላ ግብ አስቆጥረዉ የነበረ ቢሆንም ከጨዋታ ውጭ ተብሎ ተሽሮባቸዋል። አሁንም በተደጋጋሚ ማጥቃታቸዉን የቀጠሉት መቻሎች ዳግም በ35ተኛዉ ደቂቃ ላይ በቺጂኦኬ አማካኝነት ድንቅ የግብ ሙከራ አድርገዉ የነበረ ቢሆንም የግቡ ቋሚ መልሶባቸዋል ።

በተቃራኒው ያን ያህል የግብ ሙከራ ዕድል መፍጠር ያልቻሉት ሻሸመኔ ከተማዎች በአንፃሩ በሂደት ወደ ጨዋታዉ መግባት ቢችሉም ተጠቃሽ የግብ ሙከራ ሳያደርጉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል ። ከዕረፍት መልስ አንደ መጀመሪያዉ አጋማሽ ሁሉ በተመሳሳይ የጨዋታ መንገድ በቀጠለዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ በ55ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሽመልስ በቀለ ግብ ጠባቂዉን አልፎ ድንቅ ሙከራ ቢያደርግም ተከላካዩ የአብስራ አውጥቶበታል።

የጨዋታዉ ደቂቃ እየገፋ በሄደ ቁጥር ይበልጥኑ እንቅስቃሴዉን እየተቆጣጠሩ የሄዱት መቻሎች በ69ነኛዉ ደቂቃ ላይ በግቡ ባለቤት ከንዓን ማርክነህ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ማድረግ ቢችሉም ኳሷ ለጥቂት ወጥታባቸዋለች። ያን ያህል በሙከራዉ ረገድ ደካማ የነበሩት ሻሸመኔዎችም ተጨማሪ አደጋዎችን መፍጠር ሳይችሉ ጨዋታዉ በመቻል 1ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሪነቱን ሲረከብ ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል !!
Next Article በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አንደኛ ዙር የመጨረሻ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ሲያሳካ ፤ ነብሮቹ እና ሀይቆቹ አቻ ተለያይተዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

ሀትሪክ ጋዜጣ

hatricksport team By hatricksport team 9 years ago
የ2010 ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ 2ኛ ሳምንት የምድብ ሀእናለ ውጤቶችን ይመልከቱ
የጨዋታ ዘገባ | አርባምንጭ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ጨዋታቸውን በአቻ ውጤት አጠናቀዋል
ፉአድ ፈረጃ የጣና ሞገዶቹን ተቀላቅሏል!!
በትግራይ ዋንጫ መቐለና ደደቢት ተጋጣሚያቸውን በማሸነፍ ጀምረዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?