By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያ ቡና ሀምበሪቾ ዱራሜን በሰፊ የግብ ልዩነት ሲያሸንፍ ፤ ሀዋሳ ከተማም ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሀምበሪቾ ድራሜሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችሀዋሳ ከተማ

ኢትዮጵያ ቡና ሀምበሪቾ ዱራሜን በሰፊ የግብ ልዩነት ሲያሸንፍ ፤ ሀዋሳ ከተማም ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሀያ ስድስተኛ ሳምንት የመጨረሻ ዕለት ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ሀምበሪቾ ዱራሜን በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ችሏል።

ቀን ዘጠኝ ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ዳንኤል ግርማይ መሪነት በጀመረዉ ጨዋታ ሁለቱም ክለቦች ይዘዉት የመጡትን የጨዋታ መንገድ ለመተግበር እና እንቅስቃሴያቸውን ለማስቀጠል ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን በእንደዚህ አይነት እንቅስቃሴ በጀመረዉ ጨዋታም ኳስ ተቆጣጥረዉ ለመጫወት ይሞክሩ የነበሩት ቡናማዎቹ በ16ተኛዉ ደቂቃ ላይ ጨዋታዉን መምራት ጀምረዋል። በዚህም የሀምበሪቾዉ ተከላካይ ሙና በቀለ ኳስ በዕጅ መንካቱን ተከትሎ የተሰጠዉን ቅጣት ምት አማኑኤል ዮሐንስ ወደ ግብነት መቀየር ሲችል ፤ ተጫዋቹም በቀይ ካርድ ከሜዳ ተወግዷል።

ተጫዋች ገና በጊዜ በቀይ ካርድ ከወጣባቸዉ በኋላ በጎዶሎ ለመቀጠል የተገደዱት ሀምበሪቾዎች በአብዝሀኛዉ የመጀመሪያው አጋማሽ ያን ያህል ጫና ፈጥረዉ ሙከራ ማድረግ ሳይችሉ በተቃራኒው በ32ተኛዉ ደቂቃ ላይ ተጨማሪ ግብ አስተናግደዋል። በዚህም አማኑኤል አድማሱ ከመሐመድ ኑር ናስር የተሻገረለትን ኳስ በተከላካዮች አለመግባባት አግኝቷት ወደ ግብነት መቀየር ችሏል።

- ማሰታውቂያ -

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ በሁለተኛዉ አጋማሽም ቡናማዎቹ ይበልጥኑ ጫና ፈጥረዉ ሲጫወቱ በ52ተኛዉ ደቂቃ ላይም መሪነታቸዉን ወደ ሶስት ከፍ አድርገዋል። በዚህም ከመሐመድ ኑር ናስር የተቀበለዉን ኳስ አንተነህ ተፈራ በቀጥታ ወደ ግብ በመምታት ግብ ማስቆጠር ችሏል። ከዚች ግብ መቆጠር ከሀያ ደቂቃዎች በኋላም ቡናማዎቹ አራተኛ ግብ አግኝተዋል። በዚህም ሳጥን ዉስጥ አማኑኤል የመታትን ኳስ የግብ ዘቡ ሲመልሳት በቅርብ ርቀት ያገኛት መሐመድ ኑር ወደ ግብነት መቀየር ችሏል።

ቡናማዎቹ አራተኛ ግብ ካስቆጠሩ ከሁለት ደቂቃዎች በኀሏ ደግሞ በአጠቃላይ በሙሉ ደቂቃዉ የጨዋታ ብልጫ የተወሰደባቸዉ ሀምበሪቾዎች በአላዛር አድማሱ አማካኝነት ግብ ማግኘት ችለዉ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ፤ በ88ተኛዉ ደቂቃ ላይ ጫላ ተሽታ ከርቀት ድንቅ ግብ በማስቆጠር የቡናማዎቹን የግብ መጠን ወደ አምስት ከፍ ሲያደርግ በ90ናኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ መሐመድ ኑር ናስር ተጨማሪ ግብ አስቆጥሮ መርሐግብሩን ኢትዮጵያ ቡናዎች 6ለ1 እንዲያሸንፉ አስችሏል።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ በሜዳዉ እና በደጋፊዉ ፊት ሀድያ ሆሳዕናን 2ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በተመጣጣኝ የጨዋታ እንቅስቃሴ አመሻሽ 12:00 ሰዓት ሲል በጀመረዉ ጨዋታ ላይም ገና በጊዜ በአስረኛዉ ደቂቃ ሀይቆቹ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማግኘት ችለዋል። በዚህም በመልሶ ማጥቃት የተገኘዉን ኳስ የመስመር ተጫዋቹ እዮብ አለማዩ ይዞ ገብቶ ለአጥቂዉ እስራኤል እሸቱ አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል ።

ከግቧ መቆጠር በኋላ በቶሎ መልስ ለመስጠት የሞከሩት ሀድያዎች በዳዋ ሁቴሳ አማካኝነት በ13ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ አስቆጠሩ ተብሎ ሲታሰብ ያመከኑት እድል አስቆጪ ነበር ፤ በተመጣጣኝ የሚባል የመሐል ሜዳ ፉክክር በቀጠለዉ ጨዋታም በ22ተኛዉ ደቂቃ ላይ አሊ ሱለይማን ጥሩ የግብ ዕድል አግኝቶ ኳሷን ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን የግብ ዘቡ ያሬድ ኳሷን እንደምንም ይዟል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ ተጨማሪ ሙከራዎችን ሳንመለከት አጋማሹ ሲጠናቀቅ ፤ ከዕረፍት መልስ ግን ተሻሽለዉ የገቡት ሀድያዎች በ51ኛዉ ደቂቃ አቻ መሆን ችለዋል ። በዚህም ከሳጥኑ ጠርዝ አካባቢ ወደ ግራ መስመር በኩል የተሰጠዉን የቅጣት ምት ኳስ ዳዋ ሁቴሳ በግሩም ሁኔታ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን ወደ ጨዋታው መመለስ ችሏል።

በዚህ ሂደት በተመጣጣኝ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በቀጠለዉ ጨዋታ በ68ተኛዉ ደቂቃ ላይ በሜዳዉ የቀኝ መስመር በኩል አሊ ሱለይማን ወደ ዉስጥ ሲቀንሰዉ ኳስ በሀድያዉ ተከላካይ ከድር ኩልባሊ አማካኝነት በዕጅ መነካቱን ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት ራሱ አሊ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡ ሀዋሳ ከተማ ጨዋታዉን 2ለ1 እንዲያሸንፉ አስችሏል።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዋንጫዉ የተቃረበበትን ድል ሲያስመዘግብ ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስም ከ7 ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል !!
Next Article አቶ አብነት ገ/መስቀል ከእስር ተለቀቁ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችኢትዮጵያን በውጪ

ቢንያም በላይ ለክለቡ ሲይሪያንስካ የዓመቱ ሁለተኛ ግቡን አስቆጠረ

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 7 years ago
በኢትየጵያ ፕሪምየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ይደረጋሉ።
አፄዎቹ የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫን አሸነፋ
ሶስቱ የትግራይ ክለቦች መቅረታቸው ተረጋገጠ
“የቡድኔ ተጫዋቾችና ደጋፊው ያደረጉልኝ ውለታ በህይወት እንኳን የሚከፈል አይደለም”አሰልጣኝ ዘማሪያም ወ/ጊዮርጊስ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?