By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: መቻል ከሻሸመኔ ከተማ እንዲሁም ባህርዳር ከተማ ከወላይታ ዲቻ ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት ደምድመዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የጨዋታ ዘገባመቻልሻሸመኔ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችባህርዳር ከተማ

መቻል ከሻሸመኔ ከተማ እንዲሁም ባህርዳር ከተማ ከወላይታ ዲቻ ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት ደምድመዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ ስድስተኛዉ ሳምንት ሁለተኛ ዕለት ጨዋታ መቻል እና ሻሸመኔ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል።

ቀን ዘጠኝ ሰዓት ሲል በተጀመረዉ እና የመቻልን የኳስ ቁጥጥር የበላይነት ባስመለከተን የጨዋታዉ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ በተቃራኒው በኳስ ቁጥጥሩ ብልጫ የተወሰደባቸዉ ሻሸመኔ ከተማዎች ምንም እንኳን ወደ ኋላ አፈግፍገዉ በአብዝሀኛዉ መከላከል ላይ ያዘነበለ የጨዋታ መንገድ ይከተሉ እንጅ ወደ ተጋጣሚ ቡድን ሶስተኛዉ የሜዳ ክፍል አልፎ አልፎ በመድረስ ረገድ ግን የሚታሙ አልነበሩም።

በዚህ ሁነት በጀመረዉ ጨዋታ ብልጫ የነበራቸዉ መቻሎች ከቀኝ መስመር በኩል ግርማ ዲሳሳ አሻምቶት ከንዓን ማርክነህ በግንባሩ በገጨዉ ኳስ ሙከራ ማድረግ የጀመሩ ቢሆንም ፤ ነገር ግን በ30ኛዉ ግብ ተቆጥሮባቸዋል። በዚህም አማካዩ ሙልጌታ ወልደየስ ያቀበለዉን ኳስ የፊት መስመር ተጫዋቹ አብዱልቃድር ናስር በሚገርም ብቃት ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን ሻሸመኔ ከተማ መሪ ማድረግ ችሏል።

ከዚች ግብ መቆጠር በኋላ ተጋግሎ በቀጠለዉ ጨዋታ ሁለቱም ክለቦች ተደጋጋሚ ሙከራዎችን አድርገዉ አጋማሹ ሊጠናቀቅ ሁለት ደቂቃዎች ሲቀሩት ግን ሻሸመኔ ከተማዎች ሁለተኛ ግብ በአማካዩ ሙልጌታ ወ/ጊዮርጊስ አማካኝነት አስቆጥረዉ መሪነታቸዉን ወደ ሁለት ለዜሮ ከፍ ቢያደርጉም ፤ በ45+1 ላይ ግን መቻሎች በሳሙኤል ሳሊሶ አማካኝነት ያሻሙትን ኳስ ተከላካዮች በሚገባ ማፅዳት አለመቻላቸዉን ተከትሎ በረከት ደስታ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቦቹ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስ ጨዋታዉ በተመሳሳይ ቴምፖ ቀጥሎ ሻሸመኔ ከተማዎች በሙሉጌታ ወ/ጊዮርጊስ እና ማይክል ኔልሰን አማካኝነት ተከታታይ ሙከራን ማድረግ ቢችሉም በ57ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን የአቻነት ግብ ተቆጥሮባቸዋል። በዚህም ከቀኝ መስመር በኩል የመጣለትን ኳስ አማካዩ ሽመልስ በቀለ ለአጥቂዉ ምንይሉ ወንድሙ ወደ ኋላ አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን አቻ አድርጓል።

ግብ ካስቆጠሩ በኋላ ጫና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉት መቻሎች በከንዓን ማርክነህ እና አጥቂዉ ምንይሉ አማካኝነት ድንቅ ሙከራዎችን ካደረጉ በኋላ በመጨረሻዉ ደቂቃ ግብ ቢያስቆጥሩም ግብ ጠባቂዉ ላይ ጥፋት መሰራቱን ተከትሎ ግቡ ተሽሮ ጨዋታዉ ሁለት አቻ በሆነ ዉጤት ተገባዷል።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ ከወላይታ ዲቻ ጋር መርሐግብራቸዉን ያለ ግብ በአቻ ዉጤት ፈፅመዋል ።

በዋና ዳኛ ቢኒያም ወርቅ አገኘሁ ፊሽካ የምሽት 12:00 ሰዓት ሲል በጀመረዉ ጨዋታ የጣና ሞገዶቹ ባህርዳር ከተማዎች በኳስ ቁጥጥሩ የተሻለ ብልጫ በመዉሰድ ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ በተቃራኒው ተጋጣሚያቸዉ የጦና ንቦቹ ወላይታ ዲቻዎች ደግሞ ገና ከጅምሩ ወደ ራሳቸዉ የግብ ክልል አፈግፍገዉ በመጫወት አልፎ አልፎ በሚገኙ የመልሶ ማጥቃት ኳሶች አደጋዎችን ለመፍጠር ሲጥሩ ተስተውሏል።

በዚህ የታክቲክ ሂደት ጅማሮዉን ባደረገዉ ጨዋታ ላይም በ18ተኛዉ ደቂቃ ላይ ድንቅ ሙከራ ተደርጓል። በዚህም ከቀኝ መስመር በኩል የተገኘዉን የቅጣት ምት ኳስ ፍራኦል መንግስቱ በቀጥታ ወደ ግብ መትቶ አግዳሚዉ የመለሰበት አጋጣሚ በባህርዳሮች በኩል የተደረገ አስቆጪ ሙከራ ነበር ፤ በአጋማሹም የጦና ንቦቹ የጠራ የግብ ዕድል ሳይፈጥሩ ቡድኖቹ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስም ቡድኖቹ እንደ መጀመሪያዉ አጋማሽ ሁሉ በተመሳሳይ የጨዋታ መንገድ ቀጥለዉ የጠሩ የግብ ሙከራዎችን ለመመልከት ሳንችል ቀርተናል ፤ ጨዋታዉ ሊጠናቀቅ አስር ያህል ደቂቃዎች በቀሩበት ወቅት ግን ባህርዳር ከተማዎች በሀብታሙ ታደሰ አማካኝነት ጥሩ የግብ ሙከራ ቢያደርጉም ነገር ግን የገብ ዘቡ ቢኒያም ገነቱ በጥሩ ቅልጥፍና ኳስ ተቆጣጥሯታል። አጠቃላይ በጨዋታዉ ቀሪ ደቂቃዎች ግብ ሳንመለከት መርሐግብሩ ያለ ግብ 0ለ0 ተጠናቋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን በሊጉ የሀያ ስድስተኛ ሳምንት መርሐግብር ወሳኝ ድል አሳክተዋል !!
Next Article ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዋንጫዉ የተቃረበበትን ድል ሲያስመዘግብ ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስም ከ7 ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች

አሚን ነስሩ መቐለ ከተማን ተቀላቀለ

hatricksport team By hatricksport team 8 years ago
ጌታነህ ከበደ(ሰበሮም) የዮርዳኖስ አባይ ሪከርድ ለመጋራት ታላቅ ግስጋሴ ላይ ይገኛል
“በዛሬው ቡድናችን ላይ ጨዋታውን መቆጣጠር የሚችሉ ተጫዋቾች እና አስፈሪ የአጥቂ ክፍል ነበረን” አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ “የተስማሙት በአስተዳደር ላይ ያሉ ሰዎች ናቸው ፤ እኛ አሰልጣኞች ተሰብስበን አይደለም” አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ
የመቻል ስፖርት ክለብ የግብ ጠባቂ አሰልጣኞች ስልጠና ሊሰጥ ነው….
የጨዋታ ቅድመ-ዕይታ | መቐለ 70 እንደርታ ከ ፋሲል ከነማ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?