ቀን 10:00 ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ሄኖክ አበበ መሪነት በጀመረዉ የዕለቱ ጨዋታ ያን ያህል ማራኪ የሚባል የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ መመልከት ያልተቻለ ሲሆን ሁለቱም ክለቦች በአብዛኛው ኳስን በመቆጣጠር በጨዋታዉ አንዳች ነገር ለመፍጠር ሲሞክሩም ተስተውሏል።
አንዳችም ኢላማዉን የጠበቀ ሙከራ ባልተደረገበት የመጀመሪያው አጋማሽ በቀኝ መስመር በኩል ፀጋየ ብርሀኑ ክሮስ አድርጎ የነበረዉን ኳስ ብርሀኑ በቀለ በቀጥታ በጭንቅላቱ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ወደ ውጭ ወጥታለች።
በጨዋታው መሐል በ25ተኛዉ ደቂቃ ላይም የወላይታ ዲቻዉ ተከላካይ መልካሙ ጉዳት አስተናግዶ ከሜዳ የወጣበት አጋጣሚ በአጋማሹ የተፈጠረ ተጠቃሽ ሁነት የነበረ ሲሆን ፤ ከዚህ በተጨማሪ ግን ይህ ነዙ የሚባል እንቅስቃሴ ሳንመለከትበት አጋማሹ ፍፃሜዉን አጊኝቷል።
- ማሰታውቂያ -
ሁለተኛዉ አጋማሽ እንደ መጀመሪያዉ አጋማሽ ሁሉ በሁለቱም ክለቦች በኩል በተቀዛቀዘ የጨዋታ እንቅስቃሴ ቀጥሎ የነበረ ሲሆን በ78ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን በመርሐግብሩ በተደረገ የመጀመሪያ ኢላማዉን የጠበቀ ሙከራ ግብ ተቆጥሯል። በዚህም ከግራ መስመር በኩል ሄኖክ ኢሳያስ ያሻማዉን ኳስ ያገኘዉ ተመስገን በጅሮንድ በግንባሩ በመግጨት ኳሷን መረብ ላይ አሳርፎ ክለቡን መሪ አድርጓል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም በ94ኛዉ ደቂቃ ላይ ናትናኤል ናሲሮን በሁለተኛ ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቶ ጨዋታዉ በወልቂጤ ከተማ 1ለዐ አሸናፊነት ተጠናቋል።
* በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ምሽት አንድ ሰዓት ላይ በተደረገዉ ጨዋታ የአሰልጣኝ በፀሎት ልዑል ሰገድ ቡድን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሊጉ መሪ መሆን የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል ።
ምሽት አንድ ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ሚካኤል ጣዕመ ፊሽካ እና በዝናባማ አየር ታጆቦ በጀመረዉ የምሽቱ መርሐግብር ገና በመባቻዉ ሀምበሪቾ ዱራሜዎች በአዲሱ ጋናዊ ፈራሚያቸዉ አብዱልከሪም ንጉዱዋ አማካኝነት ከኋላ በተጣለ ኳስ ጥሩ የግብ ዕድል መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ ፍሬዉ ጌታሁን በጥሩ ቅልጥፍና ኳሷን ይዟታል።
በይበልጥ ኳሱን ለተጋጣሚ ቡድን በመስጠት በመልሶ ማጥቃት ዕድል ለመፍጠር ሲጥሩ የነበሩት ለምበሩቾዎች ዉጥናቸዉ ሰምሮ በ ደቂቃ ላይ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ምናሴ ብራቱ ከማዕዘን ያሻገረዉን ኳስ በቀጥታ አልዓዛር አድማሱ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ተጋጣሚ ቡድን ግብ ካስቆጠረባቸዉ በኋላ በቶሎ ወደ ጨዋታ ለመመለስ ጥረት ማድረግ የጀመሩት ባንኮች በመጀመሪያው አጋማሽ ከ30ኛዉ ደቂቃ በኋላ በኤፍሬም ታምራት እና ባሲሩ ዑመር አማካኝነት ድንቅ የግብ ዕድል ቢፈጥሩም ሳይሳካላቸዉ ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።
ከዕረፍት መልስ ሙሉ ለሙሉ ማለት በሚቻል መልኩ ብልጫ መዉሰድ የቻሉት ባንኮች በ53ተኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ግብ አግኝተዋል ፤ በዚህም አቤል ዘዉዱ ባሲሩ ዑመር ላይ የሰራዉን ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት አዲስ ግደይ ወደ ግብነት መቀየር ችሏል። የአቻነት ግብ ካገኙ ከ10 ደቂቃዎች በኋላ ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች ወደ መሪነት ተሸጋግረዋል። በዚህም ከቅጣት ምት ፉዓድ ፈረጃ ያሻማዉን ኳስ አማንኩዋ በግንባሩ ገጭቶ በማስቆጠር ክለቡን መሪ አድርጓል።
የባንኮችን ጫና መቋቋም ያልቻሉት ሀምበሪቾዎች በ72ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሶስተኛ ግብ ተቆጥሮባቸዋል። በዚህም ምናሴ ኪቲካ ላይ የሰራዉን ጥፋት ተከትሎ ፍፁም ቅጣት ምቱን አዲስ ግደይ ወደ ግብነት መቀየር ችሏል። ከሁለት ደቂቃዎች በኋላም ተቀይሮ የገባዉ ኪቲካ ጀማ ያቀበለዉን ኳስ ሳይመን ፒተር ወደ ግብነት በመቀየር መሪነታቸዉን ወደ አራት ለአንድ ከፍ አድርገዉ የነበረ ሲሆን ፤ በመጨረሻም ተቀይሮ የገባዉ ዳዊት ዮሐንስ በቀላል ንክኪ ድንቅ ጎል አስቆጥሮ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መርሐግብሩን 5ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።