By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታም ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተገባዷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችወልቂጤ ከተማ

የጨዋታ ዘገባ | የዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታም ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተገባዷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 3 years ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ24ተኛ ሳምንት መርሐግብር ሁለተኛ ዕለት ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና እና ወልቂጤ ከተማ ጨዋታቸዉን ያለ ግብ በአቻ ውጤት አጠናቀዋል።

ተመጣጣኝ በሚባል የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በጀመረው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም የአሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ ቡድን ሀድያ ሆሳዕና በፈጣን የመስመር ላይ እንቅስቃሴዎች የተሻለ ነገርን ለመፍጠር ሲጥሩ ፤ በተቃራኒው ወልቂጤ ከተማዎች ደግሞ የመሐል ክፍሉን ተቆጣጥረዉ ወደ ሳጥን ለመድረስ እና ግብ ለማስቆጠር ሲጥሩ ተስተውሏል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም በ16ተኛዉ ደቂቃ ላይ ተከላካዩ ፍሬዘር ካሳ የኋላሸት ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ ከሜዳ በቀይ ካርድ ተሰናብቷል ፤ በዚህም ተጫዋቹ በሰራዉ ጥፋት የተገኘዉን ቅጣት ምትም ጌታነህ ከበደ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት በግቡ አናት ላይ ወጥታለች።

- ማሰታውቂያ -

የቁጥር ብልጫ እና የጨዋታ ብልጫ መውሰድ የቻሉት ክትፎዎቹ በ29 ነኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ ጌታነህ ከበደ ከግራ መስመር በኩል ወደ ግብ የላከዉን ኳስ ተከላካዩ ብርሀኑ በቀለ ጨርፎ አውጥቶታል። በጎዶሎ ተጫዋች ሲንቀሳቀሱ የነበሩት እና በመጠኑም ቢሆንም ብልጫ የተወሰደባቸዉ ሀድያዎች በ32ተኛዉ ደቂቃ ላይ የመጀመሪያ ሙከራ ማድረግ ችለዋል። በዚህም ብርሀኑ በቀለ ከመሐል ሜዳ በቀጥታ ወደ ግብ የላካትን የቅጣት ምት ኳስ ግብ ጠባቂዉ ጀማል ያዘዉ ተቆጣጥሯታል።

ከዚች የቅጣት ምት ሙከራ ከሰባት ደቂቃም በኋላም በ36ተኛው ደቂቃ ላይ ሄኖክ አርፌጮ ከግራ መስመር በኩል ወደ ሳጥን ያሻማዉን ኳስ ግርማ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ሲሆን ግብ ጠባቂዉ ጀማል ጣሰዉም ኳሷ አምልጣዉ የነበረ ቢሆንም ክትፎዎቹ እንደምንም ተረባርበዉ ኳሷን አውጥተዋል።

ከዕረፍት መልስ በተጋጣሚያቸው ላይ ያለውን የቁጥር ማነስ ተጠቅመዉ ግብ ለማስቆጠር ሲጥሩ የነበሩት እና በአብዛኛው የጨዋታ ወቅት ላይ ግን በርከት ያሉ የግብ ዕድሎችን በችኮላ ሲያመክኑ የነበሩት ወልቂጤ ከተማዎች በ69ነኛዉ ደቂቃ ላይ ከግራ መስመር በኩል መነሻዉን ያደረገን ኳስ አጥቂዉ ጌታነህ ከበደ በቀጥታ ወደ ግብ ሲሞክር ግብ ጠባቂዉ በሚመልስበት ወቅም በጥሩ አቋቋም ላይ ይገኝ የነበረዉ አቤል ነጋሽ በድጋሚ ኳሷን ወደ ግብ ቢልክም በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ የግብ ዘቡ ፔፔ ሰይዶ በድጋሚ ኳሷን አውጥቷታል።

በተቃራኒው በአጥቂዉ ጌታነህ ከበደ ፣ የኋላሸት እና አለቤል የመሳሰሉ ተጫዋቾች ተደጋጋሚ ሙከራ ሲደረግባቸዉ የነበሩት ነብሮቹ ገና ከጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች አንስቶ በጎዶሎ ተጫዋች ሲጫወቱ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን በአብዝሀኛዉ በመከላከሉ ስራ ላይ ተጠምደዉ የነበሩት ሀድያዎች በሙሉ ዘጠና ደቂቃው ግብ ሳይቆጠርባቸዉ የምሽቱ ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የአርባምንጭ ከተማ እና የወላይታ ድቻ ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል
Next Article “እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ አሰልጣኝ ሆኜ ሳይሆን በተጨዋችነት ሜዳ ውስጥ ግብጽን መፋለም እመርጥ ነበር” ኢንስትራክተር ዳንኤል ገ/ማሪያም / አዲሱ የዋሊያዎቹ አሰልጣኝ /

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዋልያዎቹየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንዜናዎች

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውላቸውን አራዘሙ

hatricksport team By hatricksport team 3 years ago
ጌታነህ ከበደ ፈረሰኞቹን ተቀላቅሏል
L’Éthiopie bat l’Egypte et devenue présidente de l’ACNOA – Zone V
“በዝርክርክነትና በማን አለብኝነት በሚሰሩ ስራዎች የመጫወት እድሌን ተነፍጌያለሁ” መሳይ አያኖ/ሲዳማ ቡና/
ሲዳማ ቡና የሊግ መሪነቱን ሲያጠናክር ምድረ ገነት ሽረ እና ኢትዮጵያ ቡናም አሸንፈዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?