By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን ረቷል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን ረቷል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

በ26ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን 2 – 1 ረቷል ።

ሀድያ ሆሳዕናዎች ባህር ዳር ከተማን በረቱበት ጨዋታ ላይ በነበረው አሰላለፍ ላይ ምንም ለውጥ ሳያደርጉ ወደ ጨዋታው ሲገቡ ከለገጣፎ ለገዳዲ አቻ የተለያዩት ኢትዮጵያ ቡናዎች ራምኬል ጀምስን እና መሐመድ ኑርናስርን በክዋኩ ዷህ እና አብዱልከሪም ወርቁ ተክተው ወደ ጨዋታው ገብተዋል ።

ሀዋሳ ከጣለው ዝናብ ሀዋሳ በተጀመረው የኢትዮጵያ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታ በሁለቱም በኩል ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ የግብ ዕድሎችን ለማግኘት የጣሩበት እና ጥሩ ፉክክር የታየበት ነበር ።

- ማሰታውቂያ -

በጨዋታው ሁለተኛ ደቂቃ ላይ ኢትዮጵያ ቡና በአማኑኤል ዮሐንስ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ አስቆጥረዋል ። ከግራ መስመር የተሻገረውን እና ግብ ጠባቂው ፔፔ ሰይዶ በአግባቡ ሳይቆጣጠረው የቀረውን ኳስ ተጠቅሞ የቡናማዎቹ አምበል ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ በኢትዮጵያ ቡና በኩል በፈጣን ሽግግሮች በተለይም በመስመር በኩል የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ጥረቶች ተደርገዋል ።

በሀድያ ሆሳዕና በኩል የኢትዮጵያ ቡናን የመጨረሻ የመከላከል መስመር መስበር የሚችሉ ተሻጋሪ ኳሶችን ወደ ፊት በማድረስ ሙከራዎች ለማድረግ ጥረዋል ።

ከግቡ በኋላ የተደረገው የጨዋታው ሁለተኛ ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራም ወደ ግብነት ተቀይሯል ። ኢትዮጵያ ቡና ። መስፍን ታፈሰ ።
ከግራ መስመር ከሮቤል ተክለሚካኤል የተሻማውን ኳስ በመጠቀም መስፍን ታፈሰ በ19ኛው ደቂቃ ላይ ኳስ እና መረብ አገናኝቷል ።

በ26ኛው ደቂቃ ላይ ቀዳሚ የግብ ሙከራ በሀድያ ሆሳዕና በኩል ብሩክ ማርቆስ ከሳጥን ውጪ አክርሮ ወደ ግብ የመታውን ኳስ የኢትዮጵያ ቡናው ግብ ጠባቂ በረከት አማረ መልሶታል ። ወድያውኑ በመልሶ ማጥቃት የሄደውን ኳስ መስፍን ታፈሰ ለአብዱልከሪም ወርቁ ያቀበለውን ኳስ አብዱልከሪም ወደ ግብ ሞክሮ ፔፔ ሰይዶ አውጥቶበታል ።

በጨዋታ እንቅስቃሴ በኳስ የተመታው መስፍን ታፈሰ ጨዋታውን መቀጠል ባለመቻሉ በጫላ ተሺታ ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል ።

በሀድያ ሆሳዕና በኩል በአጋማሹ ለግብ የቀረቡበትን አጋጣሚ በፈጠሩበት ሁኔታ ላይ ተመስገን ብርሀኑ ከግርማ በቀለ የተሰነጠቀለትን ኳስ ለመጠቀም ሲሞክር በረከት ቀድሞ በመውጣት የመለሰውን ኳስ ግርማ በቀለ በድጋሚ አግኝቶ ወደ ግብ ቢሎከውም ክዋኩ ዷህ ግብ ከመሆን አድኖታል ።

የመጀመሪያው አጋማሽም በኢትዮጵያ ቡና የ2 – 0 መሪነት ተጠናቋል ።

የሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሳቢ ፉክክር የታየበት ሲሆን በተለይም ባዬ ገዛኸኝን ቀይረው ያስገቡት ሀድያ ሆሳዕናዎች የተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ ያሳዩበት እንዲሁም በኢትዮጵያ ቡና በኩል በተለይም በሮቤል ተክለሚካኤል የተፈጠሩ ግልፅ የግብ ዕድሎች ያመከኑበት ነበር ።

በ50ኛው ደቂቃ ላይ ሮቤል ተክለሚካኤል ከግራ መስመር ያሻገረውን ኳስ ጫላ ተሺታ በግንባር ገጭቶ ከግቡ አናት በላይ ልኮታል ። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላም ብሩክ በየነ ከሮቤል ያገኘውን ኳስ በማይታመን ሁኔታ ሳይጠቀምበት ቀርቷል ።

ጨዋታው 57ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ ግን ከቤራዎቹ ኳስ እና መረብን አገናኝተዋል ። በፈጣን መልሶ ማጥቃት ይዘው የሄዱትን ኳስ ባዬ ገዛኸኝ ከሳጥን ውጪ አክርሮ የመታው ኳስ በግሩም ሁኔታ መረቡ ላይ አርፏል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ ሀድያ ሆሳዕናዎች አቻ ለመሆን ኢትዮጵያ ቡናዎች ደግሞ ተጨማሪ ግብ ለማግኘት ጥረቶችን ያደረጉበት ነበር ።

በጨዋታው በጉዳት ምክንያት መስፍን ታፈሰን በጉዳት ያጡት ኢትዮጵያ ቡናዎች በሁለተኛው አጋማሽ ደግሞ ተከላካያቸውን ኩዋኩ ዷህን በድንገተኛ ህመም ቀይረው ለማስወጣት ተገደዋል ። ጋናዊው ተከላካይም ህመሙ ከፍተኛ በመሆኑ በአምቡላን ወደ ሆስፒታል አምርቷል ። በምትኩም ራምኬል ጀምስ ተቀይሮ ገብቷል ።

ፈጣን የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ እያሳየ በቀጠለው ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕናዎች ተጨማሪ ግብ ለማግኘት ጥረቶችን ቢያደርጉም የቡናማዎቹ የኋላ ክፍል በቀላሉ ለማለፍ ተቸግረው ቆይተዋል ።

በመጨረሻም ቡናማውቹ በመጀመሪያው አጋማሽ ያስቆጠሯቸውን ግቦች አስጠብቀው በመውጣት ከጨዋታው ሙሉ ሶስት ነጥብ ማሳካት ችለዋል ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የጌታነህ ከበደ ሁለት ግቦች ወልቂጤ ከተማን አሸናፊ አድርገዋል
Next Article ፋሲል ከነማ ታፈሰ ሰለሞንን አገደ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስባህርዳር ከተማ

አማኑኤል ገ/ሚካኤል ወደ ፈረሰኞቹ ምንይሉ ወንድሙ ወደ ጣና ሞገዶቹ አቅንተዋል ምንተስኖት ከበደ /አፍሪካ/ ወደ ኢት.ቡና?

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ መድኅን ተከታታይ ሶስተኛ ድል አስመዝግቧል
ሎዛ አበራ የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ መሆኗ ዛሬ ይረጋገጣል
በኢትዮጵያ አዘጋጅነት የሚካሄደው የአፍሪካ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ ሻምፒዮና ተጀመረ
HATRIIK Afaan Oromoo | Qabxiiwwan ijoo Beetkiingii Pireemiyeer liigii Itoophiyaa torban 20ffaarratti galmaa’an wajjin wal qabatee
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?