የክለብ ፈቃድ አሰጣጥ መመሪያን በተመለከተ በተለይም በመስፈርት ደረጃ ክለቦች እንዲያሟሉ ከሚጠበቁባቸዉ መካከል:-
– የታዳጊዎች ቡድን ተሳትፎ
– የተጫዋቾች የሕክምና እና እንክብካቤ
– የታዳጊዎች ልማት ፕሮግራም
– የተጫዋቾች ምዝገባ
– የተጫዋቾች ቡድን አወቃቀር የመሳሰሉ መስፈርቶች በጥልቀት ዉይይት ተደርጎባቸዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድርጅታዊ እሴቶች በሚል የሊጉ አስተዳደርን በሚመለከት በጥናቱ ከተዳሰሱት ሁለት ቁልፍ እና አበይት አስተዳደራዊ ምሶሶዎች መካከል አበይት ሁነዉ በርካታ ጉዳዮች ተነስተዉበታል።
- ማሰታውቂያ -
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደርን በተመለከተ በተለይም ደግሞ በጥልቀት በተለያዩ አለም ያሉ የስፖርቱ አመራር አካላት ባለፉት አስርት አመታት እና ሁለት አስርት አመታት ከጊዜያዊ የሜዳ ላይ ድል የዘለቀ ቀጣይነት ያለዉ እና መረጋጋት የሰፈነበት የፋይናንስ አስተዳደር ለማስፈን ይበጃል የተባሉ ዘዴዎች በስፋት ዉይይት ተደርጎባቸዋል።
የክለቦች ባለቤትነት ይዞታን በተመለከተ የሀገራት ተሞክሮ ፣ የባለድርሻ አካላትን ዕይታ ፣ የአፍሪካ እግርኳስ ክለባት የባለቤትነት ይዞታ እንዲሁም የኢትዮጵያ እግርኳስ እና ነህግ ማዕቀፍ በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ዉይይት ተደርጎበታል።
በመጨረሻም በተለይ ደግሞ የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር በዋናዉ ጥናት ነጥረዉ ከወጡ ትኩረት ከሚሹ አሳሳቢ ጉዳዮች መካከል አንዱ በመሆኑ ምክንያት በስፋት የባለ ድርሻ አካላት እይታ የአገራት ተሞክሮ እና ገዢ የህግ ማዕቀፍ ተቀናብረዉ ቀርበዉ ምክረ ሀሳብ እና ዉይይት ተደርጎባቸዋልም።
ለሁለት ቀናት ዉይይት የተደረገበት ጥናትም በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ዉስጥ በመፅሀፍ መልክ ታትሞ ለእግርኳስ ቤተሰቡ እንደሚቀርብ ተገልጿል።