መነሻ ገጽ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሁለት ግቦች ልዩነት ከመመራት ተነስቶ ነጥብ ተጋርቷል
ኢትዮ-ኤሌክትሪክወልቂጤ ከተማዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሁለት ግቦች ልዩነት ከመመራት ተነስቶ ነጥብ ተጋርቷል

አጋራ
አጋራ

በሊጉ የ21ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን መርሀግብር ቀዳሚ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አስከ መጀመሪያው አጋማሽ በሁለት ግብ ልዩነት ሲመራ ቢቆይም በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠራቸው ግቦች አንድ ነጥብ ይዞ ወጥቷል ።

ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ20ኛው ሳምንት ጨዋታ በአዳማ ከተማ ሲረቱ ከተጠቀሙት ምርጥ አስራ አንድ አራት ለውጦችን ያደረጉ ሲሆን ካክፖ ቼሪፊዳይን ፣ ያሬድ የማነ ፣ ነፃነት ገብረመድህን እና ጎሜዝ ፓውል አለንን በዘሪሁን ታደለ አንዳርጋቸው ይላቅ ፣ ሙሴ ከበላ እና ስንታየሁ ወለጬ ተክተው ገብተዋል ።

በወልቂጤ ከተማ በኩል በሳምንቱ ሲዳማ ቡና ባሸነፉበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አንድ ለውጥ ብቻ በማድረግ በማቲያስ ወልደአረጋይ ምትክ ብዙአየሁ ሰይፉን አሰልፈዋል ።

የመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜን በውድድር አመቱ ለሁለተኛ ጊዜ የአሰልጣኝ ለውጥ አድርገው ወደዚህ ጨዋታ የመጡት ኢትዮ ኤሌክትሪኮች የተሻለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ያሳዩበት ነበር ።

በጨዋታው የመጀመሪያ የግብ ዕድል በስድስተኛው ደቂቃ ላይ የተመዘገበ ሲሆን አብዱራህማን ሙባረክ ወደ ግብ ክልል ያሻገረውን ኳስ የመስመር ተከላካዩ ታፈሰ ሰርካ በግንባር ገጭቶ በግብ ጠባቂው ጀማል ጣሰው ተመልሷል ።

ከአራት ደቂቃዎች በኋላ ግን በአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ የሚመሩት ወልቂጤ ከተማዎች መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ አስቆጥረዋል ።

በአስረኛው ደቂቃ ላይ አቤል ነጋሽ ከጌታነህ ከበደ የደረሰውን ኳስ ተጠቅሞ ግብ አስቆጥሯል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ ግብ የተቆጠረባቸው ኢትዮ ኤሌክትሪኮች ተጭነው በመጫወት የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገዋል ።

ነገር ግን ለረጅም ደቂቃዎች የወልቂጤ ከተማውን የግብ ዘብ ጀማል ጣሰውን የፈተነ ሙከራ ለማድረግ ተቸግረው ነበር ። ምናልባትም በአጋማሹ ሊጠቀስ የሚችል ሁለተኛ የግብ ሙከራ በ37ኛው ደቂቃ በስንታየሁ ወለጬ አማካኝነት ማድረግ ቢችሉም ጀማል ኳሱን ተቆጣጥሮታል ።

አጋማሹ ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት የቀኝ መስመር ተከላካዩ ሳሙኤልን አስፈሪ ያሻገረውን ኳስ ዘሪሁን ታደለ ጨርፎት ያገኘው ጌታነህ ከበደ የወልቂጤ ከተማን መሪነት ወደ 2 – 0 ከፍ አድርጓል ።

በዚህም ጌታህ ከበደ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 14 ማድረስ ችሏል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ቶለ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ የጣሩት ኢትዮ ኤሌክትሪኮች በ53ኛው ደቂቃ ላይ ወደ ጨዋታው የተመለሱበትን ግብ አስቆጥረዋል ።

ከስንታየሁ ወለጬ የተነሳው ኳስ በአብዱራህማን ሙባረክ በኩል አልፎ አማካዩ አብነት ደምሴ ከመረብ አሳርፎታል ።

ከ16 ደቂቃዎች በኋላም ኢትዮ ኤሌክትሪኮች ከ2 – 0 መመራት ወደ ሁለት አቻ የመጡበትን ግብ አግኝተዋል ።

አማረ በቀለ ከመስመር ያሻገረውን ኳስ አብዱራህማን ሙባረክ አግኝቶ የወልቂጤ ከተማ ተጫዋቾች ባልጠበቁት መልኩ ወደ ግብ የመታው ኳስ በጀማል ጣሰው መረብ ላይ አርፏል ።

በአጋማሹ ተቀዛቅዘወ የታዩት ወልቂጤ ከተማዎች በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ በሁነኛ አጥቂያቸው ጌታነህ ከበደ በሚመራው የፊት መስመራቸው ግብ ለማግኝት ቢጥሩም ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዋል ።

በመጨረሻም ጨዋታው 2 – 2 ፍፃሜውን አግኝቷል ።

በ22ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሰኞ ሚያዝያ 23 በ9:00 ወላይታ ድቻ ከለገጣፎ ለገዳዲ ሲጫወቱ ረቡዕ ሚያዝያ 25 በ9:00 መቻል ድሬዳዋ ከተማን ይገጥማል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...