By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ወላይታ ዲቻ በሊጉ መቆየት የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችወልቂጤ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | ወላይታ ዲቻ በሊጉ መቆየት የቻለበትን ዉጤት አስመዝግቧል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 3 years ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሀያ ዘጠነኛ ሳምንት የመጀመሪያ ዕለት ጨዋታ ወላይታ ዲቻ እና ወልቂጤ ከተማ መርሐግብራቸዉን ያለ ግብ በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል።

በዉጤት ደረጃ ለሁለቱም ክለቦች እጅግ አስፈላጊ በነበረዉ የዕለቱ ተጠባቂ መርሐግብር ሁለቱም ክለቦች ጥንቃቄ ላይ መሰረት ያደረገን የጨዋታ መንገድ ለመከተል ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን በተለይ ወላይታ ዲቻ በርከት ያሉ ተጫዋቾቹን በጉዳት ምክንያት እንደማጣቱ ምክንያት በሜዳ ላይ የነበረዉ እንቅስቃሴ ጥሩ ነበር ብሎ ማንሳት ይቻላል።

በዚህ ሂደት በጀመረዉ ጨዋታም ክትፎዎቹ ገና በጨዋታው መባቻ በ6ተኛዉ ደቂቃ ላይ ጥሩ የሚባል ለግብ የቀረበ ሙከራ ማድረግ ችለዉ ነበር በዚህም ፤ ሳሙኤል አስፈሪ ከቀኝ መስመር ያሻማዉን ኳስ የኋላሸት ሰለሞን በሚገርም ሁኔታ በግንባሩ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም የግብ ዘቡ ቢኒያም ገነቱ በጥሩ ቅልጥፍና ኳሷን አውጥቷታል።

- ማሰታውቂያ -

ከዚች ሙከራ በኋላ አሁንም በጀመሩበት መንገድ ጨዋታቸዉን የቀጠሉት ወልቂጤዎች በ25ተኛዉ ደቂቃ ላይ በድጋሚ ድንቅ የሚባል ለግብ የቀረበ ሙከራ ማድረግ ችለዋል ፤ በዚህም አጥቂዉ ጌታነህ ከበደ ከግራ በኩል ያሻማውን የቅጣት ምት ኳስ ብዙአየሁ ሰይፈ በጭንቅላቱ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ኢላማዋን ሳትጠብቅ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በመጀመሪያው አጋማሽ በሙከራ ረገድ በመጠኑም ቢሆን በወልቂጤዎች ብልጫ የተወሰደባቸዉ ዲቻዎች በአጋማሹ በቃልኪዳን ዘላለም እና ያሬድ ከበደ አማካኝነት ያደረጓቸዉ ሙከራዎች ተጠቃሽ ነበሩ ማለት ይቻላል ። የተለየ አቀራረብ ወደ ሜዳ ይዘዉ የገቡት እና ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ማድረግ የቻሉት ክትፎዎቹ በአጋማሹ መጠናቀቂያ 45ኛ ደቂቃ ላይ በአጥቂያቸዉ ጌታነህ ከበደ አማካኝነት ጥሩ የሚባል ለግብ የቀረበ ሙከራ ማድረግ ቢችሉም ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል ።

ከዕረፍት መልስ በመጠኑም ቢሆን በማጥቃት እንቅስቃሴያቸዉ ተሻሽለዉ ወደ ሜዳ የተመለሱት ዲቻዎች በፊት መስመር ተጫዋቾቻቸዉ ቃልኪዳን ዘላለም እና ያሬድ ዳዊት አማካኝነት በድጋሚ ጥሩ የግብ ዕድል መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ዕድሉን ግን ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል ።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ ላይ በ74ተኛዉ ደቂቃ ከወልቂጤ የቀኝ ማጥቃት በኩል ከአቡበከር ሳኒ የተሻማዉን ኳስ አቤል በሚገጭበት ወቅት ያሬድ ታደሰ የተጫዋቹን መለያ በመጎተቱ ምክንያት የተሰጠዉን የፍፁም ቅጣት ምት አጥቂዉ ጌታነህ ከበደ ሳይጠቀምበት ቀርቷል ።

ከፍፁም ቅጣት ምቱ መሳት በኋላ የተረበሹ የሚመስሉት እና ግብ ለማስቆጠር ወደ ጥድፊያ የገቡት ክትፎዎቹ ረጃጅም ኳሶች ከየአቅጣጫው ፊት መስመር ላይ ለሚገኙት ተጫዋቾች በመጣል አደጋ ለመፍጠር ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን ነገር ግን ዉጥናቸዉ ሰምሮ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።

በመጨረሻም በ90ኛዉ ደቂቃ ላይም ከቀኝ መስመር በኩል አቡበከር ሳኒ የግል ክህሎቱን ተጠቅሞ ወደ ሳጥን ያሻማውን ኳስ አጥቂዉ ጌታነህ ከበደ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ኢላማዋን ሳትጠብቅ ወደ ዉጭ ወጥታለች። በዚህ ሂደት የቀጠለዉ የዕለቱ ተጠባቂ መርሐግብርም ምንም አይነት ግብ ሳይስተናገድበት 0ለ0 በሆነ አቻ ዉጤት ተጠናቋል ፤ ዉጤቱን ተከትሎም ወላይታ ዲቻ በሊጉ መሰንበቱን ሲያረጋግጥ በተቃራኒው ወልቂጤ ከተማ ደግሞ በሊጉ ለመቆየት የ30ኛ ሳምንት መርሐግብሩን እንዲጠብቅ ሁኗል።

 

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የ28ኛ ሳምንት ቀሪ ጨዋታዎች ውሳኔ እና የጨዋታ ቦታ እና ሰዓት ማስተካከያ!
Next Article የትግራይ ክለቦች ያሉበትን ደረጃ ለመገምገም እና ድጋፍ ለማድረግ የታለመ ጉዞ ወደ መቀሌ ተደረገ።

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorizedሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣችን የመጋቢት 20 ቀን 2009 ዓ/ም እትሟን pdf ይመልከቱ

hatricksport team By hatricksport team 9 years ago
“እግር ኳሱ ጋር ያለው ሽኩቻና መጠላለፍ መቆም አለበት” “የእኛ ተጨዋቾች እንደ ኢትዮጵያ ብር ለሀገር ውስጥ ብቻ ነው የሚያገለግሉት እንደ ዶላር ከሀገር ውጪም መስራት አለባቸው”ግርማ ሳህሌ ከፈረንሳይ
“እንደ አንድ የጊዮርጊስ ደጋፊ ይህ ያለ ውጤት ጉዞው ዘንድሮ ቢያበቃ ደስ ይለኛል ” አሰልጣኝ ሚሎቲን ሰሬዶዬቪች ሚቾ
መቐለ 70 እንደርታ አዳማ ሲሴኮን አስፈረመ
ሎዛ አበራ በዲሲ ፓወር የጎል አካውንቷን ከፈተች
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?