መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዲሲፕሊን ውሳኔ

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ አርብ ግንቦት 6 2013 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች) ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል ።

1. ምንተስኖት ከበደ (ኢትዮጵያ ቡና) ክለቡ ከ ባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ 23 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ ላይ በ48 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ ቀይ ካርድ አይቶ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ይህንንም ተከትሎ ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት አንድ ጨዋታ እንዲታገድ ወስኗል።

2. እንዳለ ደባልቄ (ኢትዮጵያ ቡና) ከ ባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ 23 ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ ላይ በ27 ኛ ደቂቃ ላይ ዳኛን አፀያፊ ስድብ በመሳድብ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መሰረት ሶስት ጨዋታ እንዲታገድ እና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺህ/ እንዲከፍል ወስኗል።

3. ኢትዮጵያ ቡና ክለቡ ከ ባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ 23 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ ታፈሰ ሰለሞን ፣ ምንተስኖት ከበደ ፣ እንዳለ ደባልቄ ፣ ምንተስኖት ከበደ ፣ አበበ ጥላሁን ፣ አማኑኤል ዮሀንስ በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺህ/ እንዲከፍል ወስኗል፡፡

4 አማኑኤል ዮሀንስ (ኢትዮጵያ ቡና) በአምስት ጨዋታዎች ላይ የቢጫ ካርድ መመልከቱን ተከትሎ አንድ ጨዋታ እንዲታገድ እና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል ወስኗል።

5. ለአቶ ሰለሞን ታምራት (ኢትዮጵያ ቡና /የቦርድ አባል /) ሐሙስ ግንቦት 5 2013 ባህርዳር ከተማ – ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ 23 ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ በውድድር አመራሮች ላይ የዛቻና የማስፈራራት ድርጊት መፈፀማቸው በውድድር አመራሮች ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ። በመሆኑም አቶ ሰለሞን ታምራት ለፈፀሙት ጥፋት ሶስት ወር ወደ ሜዳ እንዳይገቡ እንዲታገዱ እና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 4000 /አራት ሺህ/ እንዲከፍሉ ወስኗል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...