መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ |ነብሮቹ ከአዞዎቹ ጨዋታቸዉን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!
ሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአርባምንጭ ከተማዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ |ነብሮቹ ከአዞዎቹ ጨዋታቸዉን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!

አጋራ
አጋራ

 

በአራተኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ቀን ጨዋታ የተገናኙት አርባምንጭ ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸዉን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል።

ያን ያህል ለዕይታ ማራኪ ባልነበረዉ የመጀመሪያዉ አጋማሽ አርባምንጭ ከተማዎች ረጃጅም ኳሶችን ለፊት መስመር ተጫዋቾቻቸዉ በመጣል አንዳች ነገርን ለመፍጠር ሲጥሩ በተቃራኒው ሀድያ ሆሳዕናዎች በአንድ ሁለት ቅብብል ወደ ተቃራኒ የግብ ክልል ለመድረስ ሲጥሩ ተስተውሏል።

በዚህ ሂደት የቀጠለዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም አንድም ተጠቃሽ ለግብ የቀረበ አደገኛ ሙከራ ሳይስተዋልበት አጋማሹ ይጠናቀቅ እንጅ ሀድያዎች በጥቂቱም ቢሆን ብልጫ ለመዉሰድ ሲችሉ በተለይ በአማካዮቹ ፍቅረየሱስ እና ብሩክ ማርቆስ ተደጋጋሚ ኳሶች ለአጥቂዎቹ ቢደርሱም የሀድያ የፊት መስመር ተጫዋቾች ጥሰዉ ለመግባት ሲቸገሩ ተስተዉሏል። በዚሁ የጨዋታ መንገድም ሁለቱም ክለቦች ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስ ምንም እንኳን ጥቂት የተሻሉ ነገሮች የነበሩ ቢሆንም እንደ መጀመሪያዉ አጋማሽ ሁሉ ያን ያህል በሙከራ የታጀበ ነበር ለማለት አያስደፍርም። በጨዋታው 55ኛ ደቂቃ ላይ ግን ቡጣቃ ሻመና ከግራ መስመር በኩል ያሻገራትን ኳስ ወርቅይታደስ አበበ ሲሞክር የግራ መስመር ተከላካዩ ሔኖክ አርፌጮ እንደምንም ያወጣት ኳስ በጨዋታው ተጠቃሽ የመጀመሪያ ሙከራ ነበረች ማለት ይቻላል።

ከዚህ በኋላ ሁለቱም ቡድኖች በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ተቀይረው ወደ ሜዳ በማስገባት ከጨዋታዉ አንዳች ነገርን ለማግኘት ሲሞክሩም ተስተዉሏል። በዘዚህም በጨዋታው ጥሩ መንቀሳቀስ የቻለዉ የመስመር ተጫዋቹ ቡጠቃ ሻመና ያቀበለዉን ኳስ አጥቂዉ አህመድ ሁሴን ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም በግብ ጠባቂዉ ጥረት ኳሷ ወጥታለች። በሙከራም ሆነ በጨዋታ ረገድ ደካማ የነበረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም 0ለ0 በሆነ አቻ ዉጤት ተጠናቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...