መነሻ ገጽ ኦል ኢትዮጵያ የኦል ኢትዮጵያ እግርኳስ ፕሮጀክት የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አክብሯል
ኦል ኢትዮጵያዜናዎች

የኦል ኢትዮጵያ እግርኳስ ፕሮጀክት የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አክብሯል

አጋራ
አጋራ

ከዚህ ቀደም እግርኳስን ተጫውተው ባሳለፉ እና በእግርኳስ ከፍተኛ ዕውቀት ባላቸው ባለሙያዎች የሚመራው የኦል ኢትዮጵያ የታዳጊዎች እና ወጣቶች እግርኳስ ስልጠና ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት የተመሰረተበትን የአንደኛ ዓመት ክብረበአል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል ።

መርሀ ግብሩ በዛሬው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ካለው የሰላም ቀን ጋር በማያያዝ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ጋር በመተባበር በትንሿ ስታድየም ሲደረግ በኢፌዲሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር የስፖርት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተው ታድመዋል ።

ፕሮጀክቱ በስሩ ከ300 የሚልቁ ዕድሜያቸው ከ6 – 16 ዓመት ድረስ ያሉ ተጫዋቾች በመያዝ በአበበ ቢቂላ ስታድየም ላይ የእግርኳስ ሰልጠናዎትን በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን የነገ ተተኪዎች ከማፍራት አንፃር ጠንካራ ስራዎችን በመስራት ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ።

” እግርኳስ ለሰላም ለወዳጅነት እና ለአንድነት ” በሚል መሪ ቃል በተከበረው የአንደኛ አመት በአል ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአሰልጣኞች ስታፍ ፤ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ተጫዋቾች ፤ አርቲስቶች እንዲሁም ጋዜጠኞች የተሳተፉባቸው የፉትሳል ጨዋታዎች ተደርገዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...