ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የደመቀችው የአጥቂ መስመር ተጫዋቿ ሎዛ አበራ የአሜሪካውን ማራውደርስን መቀላቀሏ ተረጋግጧል።
ክለቡ ማራውደርስ ሎዛን ማስፈረሙን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ይፋ ያደረገ ሲሆን የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድንና የምስራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሎዛ አበራ እንኳን ደህና መጣሽ ብሏታል።
ቨርጂንያ ማራውደርስ በአሜሪካ ሁለተኛው የሴቶች ሊግ እርከን የሚወዳደር ክለብ ነው።
ይህም የሎዛ ሶስተኛ የውጪ ሀገር ክለቧ ሲሆን ከዚህ ቀደም ለማልታው ቢርኪርካራ እንዲሁም ለስዊድኑ ኩንግስባካ ተጫውታ ማሳለፏ ይታወሳል።
- ማሰታውቂያ -
ሎዛ በኢትዮጵያ ለሀዋሳ ከተማ ፣ ደደቢት ፣ አዳማ ከተማና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም ከሀገር ውጪ በማልታ እና ስዊድን ሊጎች መጫወቷ ይታወቃል።