ዋሊያዎቹ ከቻን የአፍሪካ ዋንጫ ውጪ ቢሆኑም የአውሮፕላን ቲኬት ባለመገኘቱ እስካሁን ድረስ ወደ ኢትዮጵያ አለመመለሳቸው የሰሞኑ ትኩረት የሳበ ሆኗል።
ከሁለት ተከትሎ ውሮፕላን ቲኬት ተገኝቶላቸው ዛሬ ከአልጀርስ ካይሮ ከካይሮ አዲስ አበባ የሚመጡት 11 የልዑካን ቡድን አባላት ዝርዝር ታውቋል።
ከታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ መሰረት ዛሬ ወደ አዲስ አበባ የሚመለሱት የፌዴሬሽኑ ም/ል ፕሬዝዳንትና የቡድን መሪው ዶ/ር ዳኛቸው ንግሩ፣ የፌዴሬሽኑ ዋና ጸሃፊ አቶ ባህሩ ጥላሁንና አሰልጣኝ ውበቱ አባተን ጨምሮ ይሁን እንዳሻው፣ ምኞት ደበበ፣ መስዑድ መሀመድ፣ ረመዳን የሱፍ፣ ሱሊማን ሀሚድ፣ ወንድማገኝ ሃይሉ፣ ይገዙ ቦጋለ፣ ኪቲካ ጅማና ሚሊዮን ሰለሞን መሆናቸው ታውቋል።
ቀሪዎቹ ደግሞ ነገ ምሽት እንደሚመጡ የደረሰን መረጃ ያስረዳል።