By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | መቻል ወደ አሸናፊነት ተመልሷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችድሬዳዋ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግመቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | መቻል ወደ አሸናፊነት ተመልሷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 3 years ago
Share
SHARE

 

የአዳማ ቆይታ የመጨረሻ በሆነዉ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ22ተኛ ሳምንት መርሐግብር ሶስተኛ ቀን ጨዋታ የአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኙ ቡድን መቻል ድሬዳዋ ከተማን 2ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በአንድ ነጥብ እና አንድ ደረጃ ተበላልጠዉ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ደረጃ ላይ ሁነዉ የዕለቱን የቀን ዘጠኝ ሰዓት ጨዋታቸዉን ለማከናወን እና በጥሩ ደረጃ ላይ ተቀምጠዉ ደግሞ ቀጣዩ የሊጉ መርሐግብር ወደሚደረግባት ሀዋሳ ከተማ ለማቅናት ወደ ሜዳ በገቡት የሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያዎቹ አስር  ያህል ደቂቃዎች ሁለቱም ቡድኖች ያሰቡትን የጨዋታ መንገድ በሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ለመተግበር ሲጥሩ ተመልክተናል።

በተለይ የተጋጣሚ ቡድን በነፃነት ኳሶችን ተቀባብሎ አደጋ እንዳይፈጥርባቸዉ ክፍተቶችን በመዝጋት በሚገኙ አጋጣሚዎች በቶሎ ወደ ድሬዳዋ ከተማ የግብ ክልል በመድረስ ግብ ለማስቆጠር ሲጥሩ የነበሩት መቻሎች ዉጥናቸዉ ሰምሮ በ13ተኛው ደቂቃ ላይ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ከቀኝ የመቻል የማጥቃት መስመር በኩል ከበሀይሉ የተቀበለዉን ኳስ አማካዩ ከንዓን በግሩም አጨራረስ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

- ማሰታውቂያ -

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም ከግቡ መቆጠር ከአስር ደቂቃዎች በኋላ መቻል ሁለተኛ ግብ ለማስቆጠር ተቃርቦ ነበር ፤ በዚህም በዕለቱ ድንቅ ሲንቀሳቀስ የነበረዉ ከንዓን ማርክነህ ለሳሙኤል ሳሊሶ ጥሩ ኳስ አቀብሎት ተጫዋቹ ኳሷን ሳይጠቀምባት የቀረባት አጋጣሚ በመቻል በኩል የተደረገች ተጠቃሽ ሙከራ ነበረች።

የጨዋታው ደቂቃ እየገፋ በመጣ ቁጥር ጫናቸዉን አጠንክረዉ የቀጠሉት መቻሎች በ25ተኛዉ ደቂቃ ላይ ተጨማሪ ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም ለመጀመሪያው ግብ መቆጠር ቁልፍ ሚና የነበረዉ በሀይሉ ሀለይለማርያም ያቀበለውን ኳስ አጥቂዉ እስራኤል እሸቱ ወደ ግብነት በመቀየር የክለቡን መሪነት ወደ ሁለት ለዜሮ ከፍ ማድረግ ችሏል።

ወደ ጨዋታው የሚመልሳቸዉን ግብ ለማግኘት እና በጨዋታውም ተጠቃሽ ሙከራ ለማድረግ የተቸገሩ የሚመስሉት ድሬዳዋ ከተማዎች በመጀመሪያ አጋማሽ ይህ ነዉ የሚባል ተጠቃሽ ሙከራ ሳያደርጉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስ በመጠኑም ቢሆን ተሻሽለዉ የተመለሱት ድሬዳዋ ከተማዎች በኳስ ቁጥጥሩ የበላይ የነበሩ ቢመስሉም ነገር አሁንም ግልፅ የግብ ዕድል ለመፍጠር ሲቸገሩ ተስተውሏል። ያላቸዉን የሁለት ለዜሮ መሪነት አስጠብቀዉ ለመዉጣት ያለሙ የሚመስሉት መቻሎች በተቃራኒው አልፎ አልፍ ጥሩ የሚባሉ የግብ ዕድሎችን መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ቸጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዉ በተቃራኒው ግብ አስተናግደዋል።

በዚህም በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ቀይረዉ ወደ ሜዳ ያስገቡት ድሬዳዋ ከተማዎች በተለይ በ88ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከመዓዘን ምት የተገኘዉን ኳስ ጋዲሳ መብራቴ ቢሞክርም ግብ ጠባቂዉ ውብሸት እንደምንም ኳሷን ተቆጣጥሯታል ፤ መደበኛዉ ዘጠና ደቂቃ ተገባዶ በጭማሪ ሰዓት ግን ድሬዎች በሙህዲን ሙሳ አማካኝነት ግብ አስቆጥረዉ የነበረ ቢሆንም ጨዋታዉ ግን በመቻል 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል። ዉጤቱን ተከትሎ መቻል ነጥቡን 29 በማድረስ አስረኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ፤ በተቃራኒው ሽንፈት ያስተናገደዉ ድሬዳዋ ደግሞ በ27 ነጥቦች አስራ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ ቡና እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
Next Article Bility looses appeal as CAS upholds ten year ban imposed by fifa

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችኢንተርናሽናል ዳኛ ሊዲያ ታፈሰቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የኢትዮጵያ አምባሳደሯ ኢንተ. አርቢትርሊዲያ ታፈሰ ከዳኝነቱ አለም ነገ በክብር ትሸኛለች…

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 3 years ago
በአዲስአበባ ከተማ ዋንጫ የሶስተኛ ቀን ዉሎ ቡናማዎቹ ነጥብ ሲጋሩ ሀድያ ሆሳዕና ማሸነፍ ችሏል !!
“ኢትዮጵያ ቡናን ከምንም በላይ እወደዋለው ክለቡ እንጂ ግለሰቦች የበላይ ሊሆኑ አይችሉም” “ደጋፊዎቹ ቢቃወሙኝም ሆነ ቢደግፉኝ ቅር አልሰኝምተጨዋቾቹን ግን ቢያበረታቱ ደስ ይለኛል” ገዛኸኝ ከተማ / አዲሱ የኢትዮጲያ ቡና አሰልጣኝ/
ቡናማዎቹ ከተከታታይ ሶስት ጨዋታ በኋላ አቻ ሲወጡ ፤ ኢትዮጵያ መድን አሁንም ባለማሸነፍ ጉዞዉ ቀጥሏል !!
“ማሸነፍ የነበረብንን ጨዋታ በዳኛዋ ተነጥቀናል፤ ፍፁም ቅጣት ምቱ አያሰጥም” ሄኖክ አዱኛ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?