By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የተመስገን ብርሀኑ የተጨማሪ ደቂቃ ግብ ሀድያ ሆሳዕናን ለድል አብቅቷል
Share
Notification Show More
Latest News
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….
ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
“ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ
ዋልያዎቹ ዜናዎች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሀዲያ ሆሳዕናለገጣፎ ለገዳዲዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | የተመስገን ብርሀኑ የተጨማሪ ደቂቃ ግብ ሀድያ ሆሳዕናን ለድል አብቅቷል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት መርሀ ግብር የመጨረሻ ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና ነጥቡን ከመሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያስተካከለበትን ውጤት አስመዝግቧል ።

በሀድያ ሆሳዕና በኩል በአምስተኛው ሳምንት ወላይታ ድቻን ባሸነፉበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አንድ ለውጥ ብቻ አድርገው የገቡ ሲሆን ፀጋዬ ብርሀኑ ሰመረ ሀፍተይን ተክቶ የተሰለፈ ተጫዋች ነው ። በለገጣፎ ለገዳዲ በኩል ደግሞ በሳምንቱ በባህርዳር ከተማ በተረቱበት ጨዋታ ላይ ከተጠቀሙት ምርጥ 11 ሁለት ለውጦትችን በማድረግ ፍቅሩ አለማየሁን እና አንዋር አብዱልጀባር በበረከት ተሰማ እና ኦካይ ጁል ምትክ አሰልፈዋል ።

በመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሀድያ ሆሳዕና አንፃራዊ የበላይነት የነበራቸው ሲሆን በተለይም በሁለቱ ክንፎች በኩል የለገጣፎ ለገዳዲን መረብ ለማግኘት ጥረዋል ።

በለገጣፎ ለገዳዲ በኩል በቀጥተኛ ኳሶች ወደ ተገጣሚያቸው የግብ ክልሎች ለመድረስ የሞከሩ ሲሆን አጥቂው ካርሎስ ዳምጠውን ኢላማ ያደረጉ ተደጋጋሚ ኳሶችም ወደፊት ይላኩ ነበር ።

- ማሰታውቂያ -

በጨዋታው የመጀመሪያ የግብ ሙከራ በ2ኛው ደቂቃ ላይ ሲመዘገብ ለገጣፎ ለገዳዲዎች ያገኙትን የቅጣት ምት ኪሩቤል ወንድሙ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ በግብ ጠባቂው ፔፔ ሰይዶ ተይዞበታል ።

ሀድያ ሆሳዕናዎች በጨዋታው የግብ ዕድል ለመፍጠር ተቸግረው የቆዩ ሲሆን ቀዳሚ የግብ ሙከራቸውን በ25ኛው ደቂቃ ላይ አድርገዋል ። ባዬ ገዛኸኝ በረጅም የደረሰውን ኳስ እየገፋ ሄድ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ከፍ አድርጎ ወደ ግብ የላከው ኳስ ከግቡ አናት በላይ ወጥቷል ።

በጨዋታው በሁለቱም በኩል መሪ ለመሆን ጥረቶችን ቢያሳዩም የግብ ሙከራዎች አለመኖራቸው ጨዋታውን ለዕይታ ሳቢ እንዳይሆን አድርጎታል ።

የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ ተፈራ አንለይ በረጅም የተላከለትን ኳስ የሀድያ ሆሳዕና ተከላካይን አልፎ ክግብ ጠባቂው ጋር መገናኘት ችሎ የነበረ ቢሆንም ዕድሉን ሳየጠቀምበት ቀርቷል ።

የመጀመሪያው አጋማሽም ያለ ግብ ፍፃሜውን አግኝቷል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በሁለቱም ተጋጣሚዎች በኩል ከጨዋታዉ ሶስት ነጥብ ይዘው ለመውጣት ጥረቶችን ያደረጉበት ነበር ። በአጋማሹ ምንም እንኳን በኳስ ቁጥጥሩ ረገድ ሀድያ ሆሳዕናች የተሻሉ የነበሩ ቢሆንም ወደ ግብ በመድረሱ ረገድ ለገጣፎ ለገዳዲዎች አንፃራዊ የበላይነት ነበራቸው ።

በ57ኛው ደቂቃ ላይ ከቅጣት ምት ወደ ግብ የተሻገረውን ኳስ መሀመድ አበራ በግንባር ገጭቶ ለማስቆጠር ያደረገው ጥረት ሳይሰምር ቀርቷል ።

ከአራት ደቂቃዎች በኋላ ካርሎስ ዳምጠው ጥሩ አቋቋም ላይ ሆኖ የደረሰውን ኳስ የመቆጣጠር ስህተቱ ታክሎበት በሳጥን ውስጥ ግብ ጠባቂውን አልፎ ለማስቆጠር ቢጥርሞ ሳይሳካለት ቀርቷል ። በአጋጣሚው ለገጣፎ ለገዳዲዎች የፍፁም ቅጣት ምት ይገባናል ቢሉም የዕለቱ የመሀል ዳኛ በዝምታ አልፈውታል ።

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሀድያ ሆሳዕናው ግብ ጠባቂ ኳስ በረጅም ለማውጣት ሲሞክር ካርሎስ ዳምጠው ነጥቆት የነበረ ቢሆንም አጥቂው ወርቃማውን አጋጣሚ አምክኖታል ።

ሀድያ ሆሳዕናዎች በ76ኛው ደቂቃ ላይ የጨዋታው የመጀመሪያ ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራ አድርገዋል ። አምበሉ ወርቅይታደስ አበበ ከሳጥን ውጪ አክርሮ ወደ ግብ የመታውን ኳስ ግብጠባቂው ወንድወሰን መልሶታል ።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ ተጠናቆ አምስት ያህል ደቂቃዎች የተጨመሩ ሲሆን በነዚልዠህ ደቂቃዎች ላይ የለገጣፎ ለገዳዲዎቹ ወንድወሰን ገረመው እና መዝገቡ ቶላ መጋጨታቸውን ተከትሎ መዝገቡ ጨዋታውን መቀጠል ሳይችል ቀርቷል ። የተጫዋቾች ቅያሪ አድርገው ጨርሰው የነበሩት ለገጣፎ ለገዳዲዎች ቀሪዎቹን ደቂቃዎች በጎዶሎ ለመጫወት ተገደዋል ።

ተጨማሪ ደቂቃዎች አልፈው የዳኛው የጨዋታ መጠናቀቂያ ፊሽካ ድምፅ ሲጠበቅ ሀድያ ሆሳዕናዎች ተቀይሮ በገባው ተመስገን ብርሀኑ ግብ ከጨዋታው ሶስት ነጥብ ይዘው ወጥተዋል ።

ሀድያ ሆሳዕናዎች ደሰታቸውን ከገለፁ በኋላ ከዳኛው ጋር አላስፈላጊ ንትርክ ውሰጥ ገብቶ የነበረው ግርማ በቀለ በቀጥታ የቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

You Might Also Like

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….

“ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የይገዙ ቦጋለ ሁለት ግቦች ሲዳማ ቡናን ባለ ድል አድርገዋል !!
Next Article የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ዕጣ ማውጣት መርሐ ግብር ተከናወነ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችጅማ አባጅፋር

አሰልጣኝ ጸጋዬ ኪ/ማርያም ወደ ጅማ አባጅፋር?

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 3 years ago
“የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ እግር ኳሳዊ ባልሆነ መልኩ አጥተናል” ኤፍሬም ዓለሙ [ፋሲል ከነማ]
የፕርሚየር ሊግ ሼር ካምፓኒ ህጋዊ ፍቃድ አገኘ !
ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን በመርታት ወደ ሊጉ መሪነት ተመልሷል
ድሬዳዋ ከተማ ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርሟል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?