መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሊጉ ፕሬዝዳንቱንና አመራሮቹን ነገ ሊመርጥ ነው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሊጉ ፕሬዝዳንቱንና አመራሮቹን ነገ ሊመርጥ ነው

አጋራ
አጋራ

👉..መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ዳግም ይመረጡ ይሆን ..?

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር  ለቀጣዮቹ ሶስት አመታት አክሲዮን ማህበሩን በቦርድ ፕሬዝዳንትና  አመራርነት  የሚመሩ ሰባት አመራሮችን ነገ ይመርጣል።

ነገ ጠዋት በካፒታል  ሆቴል በሚደረገውና  የ16ቱ ክለቦች ተወካዮች በሚካፈሉበት  የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ ላይ  አስቀድሞ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላለማድረግና  ምርጫው በቦርድ አመራርነት ብቻ ላይ ሊያተኩር ነው ተብሎ የተነገረ ቢሆንም ምርጫው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ማካተቱን ሀትሪክ አረጋግጣለች።

ሊግ ኩባንያው በ2012 በነበረውና በአቶ ኢሳያስ ጅራና በኮሎኔል አወል አብዱራሂም ፕሬዝዳንትና ም/ል ፕሬዝዳንትነት አመራር ዘመን  ክለቦች ራሳቸው ውድድራቸውን እንዲመሩ  ፍቃድ ከተሰጣቸው ቀን ጀምሮ  ማህበሩን ከመመስረት አንስቶ ጠንካራ ስራዎችን እስከመስራት የደረሱበትን ተግባር መከወናቸው ታውቋል።

በነገው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከምርጫው ውጪ ጠቅላላ ካፒታል ማሳደግ፣  የአክሲዮኑን ህግ ማሻሻያ ላይ መወያየት፣ የምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነዱን ማጸደቅ እንደሚከናወን ሀትሪክ ያገኘችው መረጃ ያስረዳል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...