መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 3ኛ ሳምንትና የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 3ኛ ሳምንትና የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ

አጋራ
አጋራ

 

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 3ኛ ሳምንት በተደረጉ ሰባት ጨዋታዎች ስድስት ጨዋታዎች በመሸናነፍ አንድ ጨዋታ በአቻ ሲጠናቀቅ በአጠቃላይ 22 ጎሎች በ20 ተጫዋቾች ተቆጥረዋል። በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ማጣሪያ ምክንያት በሳምንቱ ያልተካሄደው ብቸኛው የባህር ዳር ከተማ እና ፋሲል ከነማ ጨዋታ በተስተካካይ ጥቅምት 19 በባህር ዳር አለም አቀፍ ስታዲየም እንደሚካሄድ ይታወቃል። በሳምንቱ 35 ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች በቢጫ ካርድ የተገሰፁ ናቸው።

የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ጥቅምት 6/2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በክለቦች ደረጃ አርባምንጭ ከተማ በሳምንቱ ጨዋታ የክለቡ ተጫዋች አቤል ማሞ ለብሶት የገባው ማሊያ ቁጥር ከተመዘገበው የተለየ በመሆኑ እንዲሁም የማሊያው ቁጥር ከተፈቀደው ቁጥር ውጪ/ከ1-50/ በመሆኑ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ በሁለቱም ጥፋቶች ክለቡ ብር 6000 ስድስት ሺህ/ እንዲከፍል ሲወሰን ሲዳማ ቡና ባደረገው ጨዋታ የክለቡ ደጋፊዎች የእለቱን ዳኛ አፀያፊ ስደብ ስለመሳደባቸው ሪፖርት የቀረበበት በመሆኑ የክለቡ ደጋፊዎች ለፈፀሙት ጥፋት ክለቡ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 50000/ሃምሳ ሺህ/ እንዲከፍል ተወስኗል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...