By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችድሬዳዋ ከተማየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 2 years ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከብሔራዊ ቡድን ጨዋታ መልስ በዛሬው ዕለት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታድየም ወደ ውድድር ሲመለስ በቀዳሚነት የተደረገው የድሬዳዋ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ጨዋታ 1 – 1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል ።

በጨዋታው ቀዳሚ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም ቡድኖች በኩል ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ፍላጎቶች የታየበት ነበር ።

ነገር ግን በአጋማሹ ድሬደዋ ከተማም ሆነ ወላይታ ድቻ ኳሶችን በእግራቸው ስር ይዘው ለመቆየት ይቸገሩ የነበረ ሲሆን በተወሰኑ አጋጣሚዎች ያደረጓቸው ጥረቶችም የተጋጣሚ የኋላ ክፍልን በመፈተን ረገድ ደካማ ነበሩ ።

በጨዋታው የመጀመሪያው የግብ ዕድል በወላይታ ድቻ በኩል የተደረገ ሲሆን በ11ኛው ደቂቃ ላይ ቢንያም ፍቅሩ ከሳጥን ውጪ ያደረገው ሙከራ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል ።

- ማሰታውቂያ -

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ የጦና ንቦቹ ተሽለው የታዩ ሲሆን በተለይም በግራ መስመር አቅጣጫ ላይ ሰብረው ለመግባት ጥረቶችን አድርገዋል ።

በ24ኛው ደቂቃ ላይም ወላይታ ድቻዎች ቀዳሚ የሆኑበትን ግብ አግኝተዋል ። የቡድኑ የፊት አጥቂ ቢንያም ፍቅሩ ለአበባየሁ ሀጂሶ አቀብሎት በፍጥነት ወደ ሳጥን በመግባት ከአበባየሁ የተሻገረለትን ኳስ በድሬዳዋ ከተማ መረብ ላይ አሳርፎታል ።

ከግቡ በኋላ ድሬዳዋ ከተማዎች ኳሱን ይዘው በመጫወት ወደ ፊት ለመድረስ ሲሞክሩ በወላይታ ድቻ በኩል የሚገኙ ኳሶችን በፍጥነት ወደ ድሬዳዋ ከተማ የግብ ክልል በማድረስ ተጨማሪ ግብ ለማከል ሲጥሩ ተስተውሏል ።

በ32ኛው ደቂቃ ላይ ድሬዳዋ ከተማዎች በጨዋታው የመጀመሪያ አደገኛ የግብ ዕድልን መፍጠር ችለዋል ።

ቻርለስ ሙሴጌ ከያሬድ ታደሰ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ላይ ሆኖ የደረሰውን ኳስ መሬት ለመሬት ወደ ግብ ሞክሮ በግብ ጠባቂው ቢንያም ገነቱ ተመልሶበታል ። የተመለሰውን ኳስ ኤልያስ አህመድ በድጋሚ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቶበታል ።

ድሬዳዋ ከተማዎች በ38ኛው ደቂቃ ላይም በአቤል አሰበ አማካኝነት ከሳጥን ውጪ በተደረገ ሙከራ ግብ ለማስቆጠር ያደረጉት ሙከራ በቢንያም ገነቱ ተመልሷል ።

ድሬዳዋ ከተማዎች በትዕግሥት ወደ ተጋጣሚ ሜዳ ለመግባት ጥረቶች በሚያደርጉበት ወቅት የሚነጠቋቸው ኳሶች በፈጣን ሽግግር ጫና እንዲፈጠርባቸው አድርጓል ።

በተደጋጋሚ በግራ መስመር ጫና ሲፈጥሩ የቆዩት የጦና ንቦቹ በ40ኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ በቀኝ መስመር በኩል ፀጋዬ ብርሀኑ ወደ ሳጥን ገብቶ ያገኘውን ኳስ ለአበባየሁ ሀጂሶ አቀብሎ አበባየሁ የመታው ኳስ ከግቡ አናት በላይ ወጥቷል ።

በ42ኛው ደቂቃ ላይም ፀጋዬ ብርሀኑ ከግራ አቅጣጫ ከዮናታን ኤልያስ የተሻገረለትን ኳስ ተቆጣጣሮ ወደ ግብ ያደረገው ሙከራ የግቡን ቋሚ ለትሞ ወጥቷል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ድሬዳዋ ከተማ ዘርዓይ ገብረስላሴ እና ተመስገን ደረሰን ቀይረው በማስገባት የማጥቃት እንቅስቃሴያቸውን ለማጠናከር ሞክረዋል ።

በተወሰነ መልኩም በተሻለ እንቅስቃሴ የጀመሩ ቢመስልም ያለቀላቸው የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ደቂቃዎችን መጠበቅ ነበረባቸው ።

በ49ኛው ደቂቃ ላይ ተቀይሮ የገባው ዘርዓይ በረጅም የደረሰውን ኳስ ፊት ለፊት ከግብ ጠባቂው ቢንያም ገነቱ ጋር ተገናኝቶ በግንባር ወደ ግብ የመታው ኳስ የግቡን አግዳሚ መቶ ወጥቷል ።

በ61ኛው ደቂቃ ላይ ድሬዳዋ ከተማ ወደ አቻ የመጣበትን ግብ አስቆጥሯል ። ተቀይሮ የገባው ተመስገን ደረሰ አሰጋኸኝ ጴጥሮስ ከቆመ ኳስ ያሻገረለትን ኳስ በግንባር ገጭቶ ከመረብ አሳርፏል ።

ከግቡ በኋላ የነበሩት የሜዳ ላይ እንቅስቃሴዎች በሁለቱም በኩል ሁለተኛውን ግብ ቀድመው ለማስቆጠር ፈጣን እንቅስቃሴ አድርገዋል ።

ነገር ግን የሶስተኛው የማጥቃት ዞን ላይ የነበራቸው እንቅስቃሴ ሁለቱንም ቡድኖች የግብ ዕድል ለመፍጠር ያስቻላቸው አልነበረም ።

በ86ኛው ደቂቃ ላይ ወላይታ ድቻዎች ምናልባትም የሚቆጩበትን እና አሸናፊ መሆን የሚችሉበትን ዕድል ቢፈጥሩም ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል ።

አበባየሁ ሀጂሶ ከሳጥን ውጪ አክርሮ ወደ ግብ የመታውን ኳስ ግብ ጠባቂው ዳንኤል ተሾመ ሲተፋው አግኝቶ ፤ ለግቡ እጅግ በቅርበት የነበረው ብስራት በቀለ ለአብነት ቢያቀብለውም አብነት የመታው ኳስ የግቡን አግዳሚ ለትሞ ወደ ውጪ ወጥቶል ።

በመጨረሻም ጨዋታው 1 – 1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል ።

በ7ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ህዳር 27 ወላይታ ድቻ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም ህዳር 30 ቀን ድሬዳዋ ከተማ ከሲዳማ ቡና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ ።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
Next Article የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችፋሲል ከተማባህርዳር ከተማሪፖርት

ፋሲል ከነማ ባህርዳር ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል

ከድር ጀማል By ከድር ጀማል 7 years ago
የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 29ኛ ሳምንት ቀሪ 1 ጨዋታ በቀጥታ /LIVESCORE/
የቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያው ዙር ጉዞ ሲዳሰስ
የ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ጅማሮ እና ቁጥሮች !
የኢትዮጵያ ኘሪሚየር ሊግ ከ2 ሳምንታት መቋረጥ በሇላ ዛሬ በአዲስ አበባና ክልል ላይ በሚካሄዱ ቀሪ ተስተካካይ ጨዋታዎች ይጀምራል፡፡
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?