የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲስፕሊን ኮሚቴ የድሬዳዋ ከተማ አለአግባብ ከስራ አሰናብቶናል በማለት ጉዳያቸው እንዲታይላቸው አቤቱታቸውን ላቀረቡት ዮናታን ከበደ ወሰኑ ማዜ እና ሀይሌ እሸቱ የሚከተሉትን ውሳኔ ወስኗል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲስፕሊን ኮሚቴ ተጨዋቾቹ ባቀረቡት አቤቱታ የወሰነላቸው ውሳኔ ድሬዳዋ ልጆቹ ላይ ያሳለፈው የስንብት ውሳኔ እንዲሻር የግልግል ኮሚቴ በማቋቋም ጉዳዮ ን በሰላም መፍታት እንዲቻል እስካሁን የተቋረጠው የተጨዋቾች ደመወዝ በ10 ቀን ውስጥ እንዲከፈልና ክፍያው የማይፈጸም ከሆነ ከፌዴሬሽኑ ምንም አይነት ግልጋሎት ክለቡ የማያገኝ መሆኑ በላከው ደብዳቤ አስታውቋል።