መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !

አጋራ
አጋራ

 

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 16ኛ ሳምንት በተደረጉ ስምንት ጨዋታዎች ስድስት ጨዋታዎች በመሸናነፍ ሁለት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል። በሳምንቱ 48 ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች በቢጫ ካርድ ሲገሰፁ ሁለት ተጫዋቾች እና አንድ የቡድን አመራር ቀይ ካርድ ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ አርብ መጋቢት 01 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዲሲፕሊን መመሪያ እና በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ደንብ መሰረተ በተጫዋቾችና ቡድን አመራሮች ላይ በተላለፉ ውሳኔዎች – ሱራፌል ዳኛቸው(ፋሲል ከነማ) ዳኛን አፀያፊ ስድብ በመሳድብ ቀይ ካርድ አይቶ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ሶስት ጨዋታ እንዲታገድና የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል፣ ዘላለም ማቲዮስ(ወላይታ ድቻ) የክለቡ የቡድን መሪ ሲሆን የዳኛን ውሳኔ በመቃወም ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ አንድ ጨዋታ እንዲታገድና የገንዘብ ቅጣት ብር 6000 /ስድስት ሺ/ እንዲከፍል፣ አብነት ደምሴ(ኢትዮ ኤሌትሪክ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ ቀይ ካርድ የተመለከተ አንድ ጨዋታ እንዲታገድ በቃሉ ገነነ(ሃዋሳ ከተማ) በክለቡ አምስት የተለያዩ ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ በመመልከቱ አንድ ጨዋታ
እንዲታገድና የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል ተወስኗል።

በክለቦች ላይም በተመሳሳይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዲሲፕሊን መመሪያ እና በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ደንብ መሰረት በተላለፉ ውሳኔዎች ኢትዮ ኤሌትሪክ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ ሃዋሳ ከተማ እና ፋሲል ከነማ የክለቦቻቸው አምስትና ከዛ በላይ ተጫዋቾች የቢጫ ማስጠንቀቂያ ካርድ በመመልከታቸው የገንዘብ ቅጣት
ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍሉ ሲወሰን ሲዳማ ቡና ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ባደረገው ጨዋታ በአረንጓዴ ቲሴራ/መታወቂያ/ የተመዘገቡትን አራት /4/ ተጫዋቾች) ቀይሮ ስለማስገባቱ ከዳኞች ሪፖርት ተረጋግጦ በክለቡ ላይ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተላልፈውበታል ።
በመሆኑም ሲዳማ ቡና ለፈፀመው ጥፋት በፕሪምየር ሊጉ የውድድር ደንብ መሰረት ምንም እንኳ ጨዋታው በድሬደዋ 2 ለ 0 አሸናፊነት ቢጠናቀቅም የዕለቱ ውጤት ተሰርዞ በፎርፌ ተሸናፊ እንዲሆን ለክለቡ ዜሮ/0/ ነጥብና ሶስት/3/ የግብ ዕዳ እንዲሁም ለተጋጣሚው ድሬዳዋ ከተማ ሶስት/3/ ነጥብና ሶስት/3/ ተጨማሪ ግብ እንዲመዘገብ ፣ በዕለቱ የተመዘገቡት ጎል አግቢዎች እንዲሰረዙ ፣ በዕለቱ የተመዘገቡት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች እንዲፀኑና የቡድን መሪው አቶ ቾምቤ ገብረ ህይወት ለ6ወር እንዲታገዱና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 25000 /ሃያ አምስት ሺህ/ እንዲከፍሉ ተወስኗል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...