መነሻ ገጽ ቁጥሮች የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ዙር ቁጥራዊ መረጃዎች – ክለቦች
ቁጥሮችቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ዙር ቁጥራዊ መረጃዎች – ክለቦች

አጋራ
አጋራ

የ2015 ዓ.ም የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር የመጀመሪያ ዙር ባሳለፍነው ረቡዕ ተጠናቆ የሁለተኛ ዙር አንድ ጨዋታም በዕለተ ሀሙስ ተካሂዷል ።

ውድድሩ መስከረም 20 በባህርዳር ዓለም ዓቀፍ ስታድየም በወልቂጤ ከተማ እና አርባምንጭ ከተማ መካከል በተደረገ ጨዋታ ጅማሮውን አድርጓል ። እስከ አምስተኛ ሳምንት ድረስ ያሉ ጨዋታዎች በባህርዳር ከተማ ከተደረጉ በኋላ ከስድስተኛ ሳምንት ጀምሮ በድሬደዋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል ።

በዚህ ዘገባችን በመጀመሪያው ዘር የተመዘገቡ የተለያዩ ቁጥራዊ መረጃዎችን ይዘንላችሁ ቀርበናል ።

በመጀመሪያው ዙር 120 ጨዋታዎች ሲደረጉ 295 ግቦች ከመረብ አርፈዋል ። ከነዚህ ጨዋታዎች መካከልም 79 ጨዋታዎች በመሸናነፍ ሲጠናቀቁ 41 ጨዋታዎች ደግሞ በአቻ ውጤት ፍፃሜያቸውን አግኝተዋል ።

ባለሜዳ ሆነው ጨዋታውን የሚያካሂዱ ክለቦች የማሸነፍ ንፃሬያቸው 27.5%(33/120) ሲሆን የእንግዳ ክለቦች ደግሞ 38.33%(46/120) ነው ።

 

– በርካታ ነጥቦችን የሰበሰበው
ቅዱስ ጊዮርጊስ – 32
– ጥቂት ነጥቦችን የሰበሰበው
ለገጣፎ ለገዳዲ – 6
– በርካታ ጨዋታዎችን ያሸነፈው
ቅዱስ ጊዮርጊስ – 9
ኢትዮጵያ መድኅን – 9
– በርካታ ጨዋታዎች ላይ አቻ የተለያየው
አርባምንጭ ከተማ – 8
– በርካታ ጨዋታዎችን የተሸነፈው
ለገጣፎ ለገዳዲ – 11
– ጥቂት ጨዋታዎችን ያሸነፈው
ለገጣፎ ለገዳዲ – 1
ኢትዮ ኤሌክትሪክ – 1
– ጥቂት ጨዋታዎች አቻ የተለያየው
ኢትዮጵያ መድኅን – 3
አዳማ ከተማ – 3
ለገጣፎ ለገዳዲ – 3
– ጥቂት ጨዋታዎች የተሸነፈው
ቅዱስ ጊዮርጊስ – 1

– አራት ክለቦች(ፋሲል ከነማ ፣ ሀድያ ሆሳዕና ፣ ሀዋሳ ከተማ እና ወላይታ ድቻ) በተመሳሳይ 5 ጨዋታዎች አሸንፈው ፣ 6 ጨዋታዎች አቻ ሲለያዩ በ4 ተሸንፈዋል ።

– ሶስት ክለቦች(ኢትዮጵያ ቡና ፣ ወልቂጤ ከተማ እና መቻል)በተመሳሳይ 5 ድል ፣ 5 አቻ እንዲሁም 5 ሽንፈት አስተናግደዋል ።

– በሊጉ 4ኛ ደረጃ ላይ በተቀመጠው ፋሲል ከነማ እና 14ኛ ደረጃ ላይ በተቀመጠው ድሬዳዋ ከተማ መካከል ያለው የነጥብ ልዩነት 4 ብቻ ነው ።

በሊጉ የ15 ሳምንታት ቆይታ 295 ግቦች ተቆጥረዋል ። ይህም ማለት በአማካይ በአንድ ጨዋታ 2.46 ግቦች ይቆጠራሉ ።

በነዚህ 120 ጨዋታዎች 15 አይነት ውጤቶች ተመዝግበዋል ። ከነዚህም መካከል ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ መድኅንን 7 ለ 1 ያሸነፈበት ጨዋታ በሰፊ ውጤት የተጠናቀቀ እና በርካታ ግቦች የተቆጠሩበት ጨዋታ ሆኖ ተመዝግቧል ።

በመጀመሪያው ዙር በቁጥር በርከት ብሎ የተመዘገበው የ1 ለ 0 ውጤት ሲሆን 21 ጨዋታዎች በዚህ ውጤት ተጠናቀዋል ።

– በርካታ ግቦች የተቆጠሩበት ሳምንት
1ኛ እና 8ኛ ሳምንታት – 23
– ጥቂት ግቦች የተቆጠሩበት ሳምንት
12ኛ ሳምንት – 8
– በርካታ ግቦችን ያስቆጠረ ክለብ
ቅዱስ ጊዮርጊስ – 32
– በርካታ ግቦች የተቆጠሩበት ክለብ
ለገጣፎ ለገዳዲ – 37
– ጥቂት ግብ ያስተናገደው ክለብ
ቅዱስ ጊዮርጊስ – 9
ሀድያ ሆሳዕና – 9
– በርካታ የፍፁም ቅጣት ምት ያገኘ ክለብ
ወልቂጤ ከተማ – 5
– በርካታ የፍፁም ቅጣት የተሰጠበት ክለብ
አዳማ ከተማ – 2
– በርካታ የፍፁም ቅጣት ምት ያስቆጠረ ክለብ
ወልቂጤ ከተማ – 5
– በርካታ የፍፁም ቅጣት ምት ያመከነ ክለብ
ኢትዮጵያ ቡና – 2
ሀድያ ሆሳዕና – 2

በመጀመሪያው ዙር 540 የቢጫ ካርዶችን 275 የቡድን አባላት (ተጫዋቾች እና የስታፍ አባላት)ተመልክተዋል ። ከነዚህ ካርዶች መካከል 515 ተጫዋቾች ሲሆኑ 25 ደግሞ ሌሎች የቡድን አባላት የመለከቱት ነው ።

23 የቡድን አባላት የቀይ ካርድ ሰለባ ሲሆኑ 16 በሁለተኛ ቢጫ 7 ደግሞ በቀጥታ የቀይ ካርድ ከሜዳ የተሰናበቱ ናቸው ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...