በአሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ እየተመሩ ለ2016 ዓ.ም የዉድድር ዘመን አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ እየቀላቀሉ እንዲሁም የነባር ተጫዋቾቻቸዉን ዉል እያደሱ የሚገኙት አዳማ ከነማዎች ለ2016 ዓ.ም የዉድድር ዘመን ዝግጅት የሚጀምሩበት ቀን ታዉቋል።
በዚህም መሰረት ነሀሴ 10 እሮብ በአዳማ ራስ ሆቴል በመሰባሰብ በማግስቱ ነሀሴ 11 ሀሙስ ዝግጅታቸዉን እንደሚጀምሩ ለማወቅ ችለናል።
- ማሰታውቂያ -
አዳማ ከተማዎች እስካሁን ድረስ ዉላቸዉን ከጨረሱ ከ11 ተጫዋቾች ጋር የተለያዩ ሲሆን እንዲሁም አዳዲስ 7 ተጫዋቾችን ማስፈረም ሲችሉ 4 ታዳጊ ልጆችን ከተስፋ ቡድን ወደ ዋናዉ ቡድን ያሳደጉ ሲሆን የ 1 ተጫዋች ዉል አድሰዋል።
አዳማ ከተማዎች ዉሉን ካደሱለት ከ1 ተጫዋች በተጨማሪ የሌላ የ1 ተጫዋች ዉል ለማደስ በአሁን ወቅት በንግግር ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ ችለናል።