በመጨረሻዎቹ ጨዋታዎች ባገኙት ዉጤት ከሊጉ የተረፉዉ ድሬደዋ ከተማ በቀጣይ አመት ቡድኑን ለማጠናከር አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ እየቀላቀሉ ይገኛሉ፤ ክለቡ ዛሬ የሶስት ተጫዋቾችን ሲያስፈርም የመስመር አጥቂዉን ሙየዲን ሙሳን ኮንትራት በሁለት አመት አድሷል።
እንዲሁም በቀጣይ የዉድድር አመት የተከላካይ መስመሩን እና የአማካይ መስመሩን ለማጠናከር በዚህ የዉድድር አመት በወልቂጤ ያሳለፉትን ቴዎድሮስ ሀሙ እና ሄኖክ አንጃዉን በሁለት አመት ኮንትራት አስፈርመዋል።
- ማሰታውቂያ -
በተጨማሪም የምስራቁ ተወካይ ድሬደዋ ከየቀድሞዉ ተጫዋቻቸዉን በዚህ የዉድድር አመት ደግሞ በይርጋ ጨፌ ቡና ያሳለፈዉን ግብ ጠባቂ ሀምዲ መሀመድን በሁለት አአመት ኮንትራት ማስፈረማቸዉ ይፋ አድርገዋል።