በ2015 ዓ.ም የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዉድድር ዘመን ላይ በ30 ሳምንት ጨዋታዎች 34 ነጥብ ብቻ በመሰብሰብ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረደዉ አርባምንጭ ከነማ የነባር የሶስት ተጫዋቾቹን ዉል አድሷል።
የ2016 ዓ.ም የውድድር ዘመን የከፍተኛ ሊግ ተሳታፊ የሆነው አርባምንጭ ከተማ እግርኳስ ክለብ አማካዩን መሪሁን መስቀሌን ፣ የአንበሉን ወርቅይታደስ አበበን እና የተከላካዩን የአንዱአለም አስናቀን ዉል አድሷል።
ክለቡ በቀጣይ ቀናትም የሌሎች ተጫዋቾችን ዉል እንደሚያድስ እና ወደ ስብስቡ አዳዲስ ተጫዋቾችን እንደሚቀላቅል ለማወቅ ችለናል።