በወጣቱ ዋና አሰልጣኝ በረከት ደሙ የሚመራው በ2016 ዓ/ም የከፍተኛ ሊጉ የአሸናፊዎች አሸናፊ ክለብ አርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በፕሪሚየር ሊጉም ጥንካሬውን ለማስቀጠል የክለቡ ነባር ተጨዋቾችን ውል የማደስ ስራ አጠናክሮ ቀጥሏል ።
በዚህም በከፍተኛ ሊጉ ክለቡን በትጋት ያገለገሉና ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ያሳደጉ የክለቡን ልጆች ውላቸውን እያደሱ ሲሆን ከነዚህም መካከል በዛሬው ዕለት
1. አበበ ጥላሁን ፦ የተከላካይ መሰመር ተጨዋችና የክለቡ አምበል
2. አሸናፊ ፊዳ፦ የተከላካይ መሰመር ተጨዋች
3. ቡታቃ ሻመና ፦ የመሃል ሜዳ ተጨዋች ውላቸውን አራዘመዋል።