የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ታዳጊ ወጣቶች ፕሪምየር ሊግ የ2014 የውድድር ዓመት የዕጣ ማውጣት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በጁፒተር ሆቴል ተካሂዷል ። በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ የመክፈቻ ንግግር የተጀመረው መርሀ ግብር በመቀጠልም የ2013 አጠቃላይ ሪፖርት በውድድር ባለሙያ ወ/ሪት ምህረት ጉታ ፣ የዳኞች ሪፖርት በዳኞች ባለሙያ አቶ ሙሉጌታ ምስጋናው ፣ የህክምና ሪፖርት በህክምና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ሳሙኤል የሺዋስ እንዲሁም የቴክኒክ እና ልማት ዳይሬክቶሬት እቅድ በአቶ እንዳለየሱስ አባተ አማካኝነት ቀርቧል።
ከሻይ እረፍት በኋላ በ2014 የደንብ ውይይት እና አጠቃላይ በውድድሩ ዙርያ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን በሚመለከታቸው አካላትም ምላሽ እና ማብራርያ ተሰጥቶባቸው የ2014 ደንብ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል ። በመቀጠልም የውድድሩ ምድቦች ፣ የጨዋታ መርሀ ግብሮች እና ውድድሮች የሚካሄዱበት ስፍራ ዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ተካሂዷል ።
በዕጣው መሰረት የምድብ ሀ ጨዋታዎች በጎንደር ከተማ የምድብ ለ ደግሞ በአሰላ ከተማ የሚካሄዱ ሲሆን የመጀመሪያ ጨዋታዎች የካቲት 12/2014 ዓ.ም የሚካሄዱ ይሆናል ።
ምድብ ሀ ( ጎንደር )
1. ሀላባ ከተማ
2. ሲዳማ ቡና
3. ሰበታ ከተማ
4. ሀድያ ሆሳዕና
5. ባህርዳር ከተማ
6. ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
7. ወላይታ ድቻ
8. አርባምንጭ ከተማ
9. አዳማ ከተማ
10. ኢትዮ ኤሌክትሪክ
ምድብ ለ ( አሰላ )
1. አዲስ አበባ ከተማ
2. ወላይታ ዞን
3. ሀዋሳ ከተማ
4. ድሬዳዋ ከተማ
5. ቅዱስ ጊዮርጊስ
6. መከላከያ
7. ኢትዮጵያ መድህን
8. ኢትዮጵያ ቡና
9. ፋሲል ከተማ

የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች
ምድብ 1
ሀላባ ከተማ ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ
ሲዳማ ቡና ከ አዳማ ከተማ
ሰበታ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ
ሀድያ ሆሳዕና ከ ወላይታ ድቻ
ባህርዳር ከተማ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ምድብ 2
ወላይታ ዞን ከ ፋሲል ከተማ
ሀዋሳ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ቡና
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ መከላከያ
ኢትዮጵያ መድን ከ ድሬዳዋ ከተማ
አስተያየት ይስጡ