መነሻ ገጽ ዜናዎች የምርጫው ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ስራውን ጀመረ
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንጠቅላላ ጉባዔ

የምርጫው ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ስራውን ጀመረ

አጋራ
አጋራ

👉…እስከ ነሀሴ 6 በስራ ላይ ይሆናል

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚቴ የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ከዛሬ ረቡዕ ጀምሮ ስራውን እንደሚጀምር ይጠበቃል።

በፌዴሬሽኑ የህግ አማካሪ በአቶ ሃይሉ ሞላ የሚመራው የአስመራጭ ኮሚቴ 26 ለስራ አስፈጻሚ 3 ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ይፋ በማድረግ ስራውን ትላንት በይፋ ጨርሷል።

በአስመራጭ ኮሚቴው መብቱ የተነፈጋቸው የሀረሪ ክልል ውክልና ያነሳባቸው አቶ ገዛኸኝ ወልዴ፣ ለሶስት የምርጫ ዘመን ተወዳድረው ለአራተኛ ጊዜ ህጉ የከለከላቸው የአፋሩ አቶ አሊሚራህ መሀመድ፣ በህጉ መሠረት በአምስት ክለቦች ያልተደገፈ መረጃ አምጥተዋል የተባሉት ሶስቱም የጋምቤላ ክልል ዕጩዎችና ሙሉ መመዘኛ አሟልቶ ባለማቅረብ እንደ ክልል የቢኒሻንጉል ጉሙዝ ከምርጫ ውጪ በመደረጋቸው ሶስት አባላት ላሉት የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ከዛሬ ሀምሌ 27-ነሀሴ 6 /2014 ድረስ ይግባኝ የመጠየቅ ዕድል ተሰጥቷቸዋል።

የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ሶስቱ አባላት ደግሞ የብሄራዊ
የስፖርት አካዳሚ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አንበሳው እንየው…በቀድሞ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ ዘመን ም/ል ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ
ብርሀኑ ከበደና የወወክማ ዋና ስራአስኪያጅ አቶ መኮንን ጤናው መሆናቸው ታውቋል።

 

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...