ዓለም አቀፍ ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ላይ እንዲዳኙ የተመረጡ ዳኞች ዝርዝር ውስጥ ተካታለች።
ከዚህ ቀደም የሴቶች የአፍሪካ እና የዓለም ዋንጫን ጨምሮ በበርካታ ውድድሮች ላይ ተመርጣ በብቃት ስታጫውት የቆየችው ዓለም አቀፍ ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ ካፍ ይፋ ባደረገው ዝርዝር በሞሮኮ አስተናጋጅነት ከሰኔ 25 ጀምሮ በሚካሄደው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ላይ በመሐል ዳኝነት ከተመረጡ 16 ዳኞች መካከል አንዷ መሆን ችላለች።
ካፍ 16 ዋና እና 16 ረዳት ዳኞችን የመረጠ ሲሆን ለቪኤአር ዳኝነት ደግሞ 8 ዳኞችን መመደቡን አስታውቋል። የካፍ የዳኝነት ዳይሬክተር ኤዲ ማይሌት ከውድድሩ አምስት ቀን ቀደም ብሎ የሚሰጥ የቅድመ ዝግጅት ኮርስ እንዳዘጋጀም ገልፀዋል ።
©EFF
አስተያየት ይስጡ