የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ውሳኔ ጸንቶባቸው ውሳኔውን ተፈጻሚ ያላደረጉ አምስት ክለቦችን ከቀጣዩ የዝውውር መስኮት ማገዱን አስታወቀ።
በፌዴሬሽኑ ዋና ጸሃፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ፊርማና ማህተም በወጣው ደብዳቤ ሁለት የፕሪሚየር ሊግ ክለቦችን ጨምሮ አራት ክለቦችን ማገዱን አሳውቋል።
በዚህም መሠረት የፕሪሚየር ሊጉ መሪ ወላይታ ድቻ በይግረማቸው ተስፋዬ፣ ሀድያ ሆሳዕና በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ፣ ከፋ ቡና በዳግም እንዳልካቸው፣ በሙሉቀን አበበ፣ በአብይ ምንዋጋውና እንዳልካቸው ዘውዴ ፤ ቤንች ማጂ ቡና ደግሞ በሚካኤል እጅጉ በቀረበባቸው ክስ የፍትህ አካላቱ የሰጡትን ውሳኔ ባለመፈጸማቸው መታገዳቸውን የሕግ አማካሪ ጠበቃና የእግርኳስ ሰፖርትኞች ሕጋዊ ወኪል የሆኑት አቶ ብርሃኑ በጋሻው ተናግረዋል።

አስተያየት ይስጡ